፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
በዓለ ጥምቀት በዓለ ቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩን የለወጠ ክስተት ነው የተፈጸመው፡፡ ወልዲያ
ታቦቱን የተሸከሙ ካህናት ራሳቸውን ስተው ወድቀዋል ምእመናን ከታቦቱ ፊት ነፍሳቸውን ሰጥተዋል፡፡ የዚህን ክስተት ሙሉ ኃላፊነት
ቤተክርስቲያናችን መውሰድ ይገባታል፡፡ ምክንያቱም የበዓላት ሥነሥርዓት አስከባሪ የቤተክርስቲያኒቱ የሰበካ ጉባዔ እያለ ከሰበካ ጉባዔው
ቁጥጥር በላይ የሆነ አንዳች ችግር ሳይፈጠር የመንግሥትን ጸጥታ አስከባሪዎች ወደቦታው መጥራት አስፈላጊ ስላልነበር ነው፡፡ ሕገመንግሥቱ
ሃይማኖት እና ፖለቲካ የተለያዩ ናቸው ሃይማኖት በፖለቲካ ፖለቲካም በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም ብሎ በደነገገበት ሁኔታ የመንግሥት
ጸጥታ ኃይሎች ከታቦቱ ፊት እንዲገኙ ማድረጋቸው የቤተክርስቲያኒቱን አባቶች ያስተቻል፡፡