Sunday, June 30, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 127

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
ምዕራፍ ፳፮።
                    ******
ዘከመ ጸለየ ኢየሱስ በጌቴሴማን።
፴፮፡ ወእምዝ ሖረ እግዚእ ኢየሱስ ምስሌሆሙ ውስተ ዓፀደ ወይን ዘስሙ ጌቴሴማን።
፴፮፡ ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን አስከትሎ ጌቴሴማን ከሚባለው ወይን ቦታ ሄደ።
ወይቤሎሙ ለአርዳኢሁ ንበሩ ዝየ እስከ ሶበ አሐውር ከሀ ወእጼሊ።
ደቀ መዛሙርቱን ከዚያ ሄጄ አስክጸልይ ድረስ ከዚህ ቆዩ አላቸው፡፡
አንድም እጼሊ ይላል እጸልይ ዘንድ፡፡
                    ******
፴፯፡ ወነሥኦሙ ምስሌሁ ለጴጥሮስ ወለ፪ሆሙ ደቂቀ ዘብዴዎስ
                    ******
፴፯፡ ሦስቱን ባለሟሎቹን አስከትሎ ሄዶ ስምንቱን በጌቴሴማኒ ትቶ፡፡
ወአኀዘ ይተክዝ ወይኅዝን፡፡
                    ******
፴፰፡ ወእምዝ ይቤሎሙ ተከዘት ነፍስየ እስከ ለሞት፡፡
                    ******
፴፰፡ ከዚህ በኋላ ለደቀመዛሙርቱ ነፍሴ እስከ መለየት ደርሳ አዘነች አላቸው፡፡
ወንበሩ ዝየ
ከዚህ      ቆዩ፡፡
ወትግሁ ምስሌየ
ከእኔ ጋር ለመኖር እንደ እኔ ተግታችሁ አመልክቱ፡፡
                    ******
፴፱፡ ወተአተተ ሕቀ እምህየ ወሰገደ በገጹ።
                    ******
፴፱፡ ከዚያ ጥቂት እልፍ ብሎ ግንባሩን ምድር አስነክቶ ሰገደ። በሉቃስ መጠነ ሙጋረ ዕብን ይላል ደንጊያ ወርውሮ እስከሚደርስበት፡፡
ወጸለየ
አመለከተ፡፡
ወይቤ ኦ አቡየ እመሰ ይትከሃል ይኅልፍ እምኔየ ዝንቱ ጽዋዕ፡፡
ያለኔ ሞት የዓለሙ ድኅነት ያለኔ ሐሣር የዓለሙ ክብር አይቻልም እንጂ የሚቻልስ ከሆነ ይህ ጽዋዓ ሞት ይለፍልኝ 
ወባሕቱ ፈቃደ ዚአከ ይኩን ወአኮ ፈቃደ ዚአየ።
ነገር ግን ያንተ ፈቃድ ይደረግ እላለሁ እንጂ የኔ ፈቃድ ይደረግ አልልም፡፡
አንድም በኔ ሞት የዓለም ድኅነት በኔ ኃሣር የዓለም ክብር የሚቻልስ ከሆነ እኔ ከሞትሁላቸው ከኔ ሞት የተነሣ ይህ ጽዋዓ ሞት ይቅርላቸው፡፡
አንድም ከኔ ለምዕመናን ይለፍላቸው እኔን አብነት አድርገው ይሙቱ።
ወባሕቱ ፈቃደ ዚአከ ይኩን ወአኮ ፈቃደ ዚአየ።
ነገር ግን የኔ ፈቃድ ከአንተ ፈቃድ ልዩ ሁኖ የኔ ፈቃድ ይሁን አልልም። የኔ ፈቃድ ከአንተ ፈቃድ ጋራ አንድ ነውና ያንተ ፈቃድ ይሁን አላለሁ እንጂ፡፡
                    ******
፵፡ ወሖረ ኀበ አርዳኢሁ፡፡
                    ******
፵፡ ወደ ደቀመዛሙርቱ ሄደ፡፡
ወረከቦሙ እንዘ ይነውሙ፡፡
ተኝተው አገኛቸው፡፡
ወይቤሎ ለጴጥሮስ ከመዝኑ ስአንክሙ ተጊሃ አሐተ ሰዓተ ምስሌየ።
ጴጥሮስን ከኔ ጋራ ለመኖር እንደ እኔ አንድ ሰዓት መትጋት ተሳናችሁ አለው፡፡
                    ******
፵፩፡ ትግሁ ወጸልዩ ከመ ኢትባኡ ውስተ መንሱት፡፡
                    ******
፵፩፡ ወደ ኃጢአት ወደ ክህደት ወደ መከራ ወደ ገሃነም እንዳትገቡ ተግታችሁ ለምኑ።
እስመ መንፈስ ይፈቅድ።
ነፍስ ሥራ ልትሠራ ትወዳለችና ትግሁ።
ወሥጋ ይደክም።
ሥጋ ግን ደካማ ነውና ኢትባኡ ላለው።
                    ******
፵፪፡ ወካዕበ ሖረ ወጸለየ።
                    ******
፵፪፡ ሁለተኛ ሂዶ አመለከተ፡፡
ወይቤ እመ ይትከሃል ይኅልፍ እምኔየ ዝንቱ ጽዋዕ እንበለ እስተዮ ይኩን ፈቃድከ። እንዳለፈው በል።
                    ******
፵፫፡ ወገብአ ካዕበ ኀበ አርዳኢሁ።
                    ******
፵፫፡ ሁለተኛ ወደ ደቀመዛሙርቱ ሄደ፡፡
ወረከቦሙ እንዘ ይነውሙ።
ተኝተው አገኛቸው፡፡
እስመ ከብዳ አዕይንቲሆሙ በድቃስ።
እንቅልፍ ጸንቶባቸዋልና በልተው ጠጥተዋልና።
                    ******
፵፬፡ ወኀደጎሙ ወሖረ ካዕበ በሣልስት ወጸለየ ኪያሁ ከመ ቃለ እንዘ ይብል።
                    ******
፵፬፡ ሦስተኛ ሂዶ ያነኑ ጸለየ ለቀረበው ካዕበ ለመጀመሪያው ሣልሰ አለ፡፡ ሦስት ጊዜ መሆኑ የሦስትነት። ቃሉ አለመለወጡ የአንድነት ምሳሌ።
                    ******
፵፭፡ ወእምዝ ገብአ ካዕበ ኀበ አርዳኢሁ።
                    ******
፵፭፡  ከዚህ በኋላ ሁለተኛ ወደ ደቀ መዛሙርቱ ሄደ።
ወይቤሎሙ ኑሙ እንከ ወአእርፉ።

ከእንግዲህስ ወዲህ ዕረፉ አላቸው፣ ጊዜው ነውና ንሣእ ሀካይ ሥጋየ መክፈልተከ እንዲል፡፡
አንድም እኔ ካስሁላችሁ ዕረፍተ ነፍስ ዕረፉ።
አንድም ይሁዳ አራት ቤት ጭፍራ ይዞ የሚመጣ ነውና አያሳርፋችሁም እንጂ ካሳረፋችሁስ ዕረፉ ለማለት።
ናሁ በጽሐ ጊዜሁ ወያገብዕዎ ለወልደ እጓለ እመሕያው ውስተ አደ ኃጥአን።
እነሆ ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስ በኃጥአን እጅ የሚያዝበት ጊዜ ደርሷል አላቸው።
                    ******
፵፮፡ ተንሥኡ ንሑር ናሁ በጽሐ ዘያገብአኒ።
                    ******
፵፮፡ የሚያሲዘኝ ይሁዳ እነሆ መጥቷል ተነሡ እንሂድ አላቸው፡፡
                    ******
ዘከመ አግብኦ ይሁዳ ለክርስቶስ ወዘከመ ተእኅዘ
፵፯፡ ወእንዘ ዘንተ ይትናገር ናሁ በጽሐ ይሁዳ ዘያገብዖ እም፲ቱ ወ፪ቱ ፩ዱ፡፡ ማር ፲፬፥፵፫፡፡ ሉቃ ፲፪፥፵፯፡፡ ዮሐ ፲፰፥፫፡፡
                    ******
፵፯፡ ይህን ሲናገር ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ ሊያሲዘው መጣ፡፡
ወመጽኡ ምስሌሁ ብዙኃን ሰብእ በመጣብሕ ወበአብትር እምኀቤሆሙ ለሊቃነ ካህናት ወለሊቃናተ ሕዝብ፡፡
ሾተል ጎመድ የያዙ ብዙ ሰዎች ከሊቃነ ካህናት ዘንድ ከእሱ ጋራ መጡ፡፡
(ሐተታ) አምስት ገበያ ሰው ይከተለዋል አግባ መልስ ብሎ ቢጣላንሳ ብለው እሳቸው ከጲላጦስ ዘንድ ይዘው ይመጣሉ እሱ ከእነሱ ተቀብሎ ይዞ መጥቷልና፡፡
                    ******
፵፰፡ ወዘያገብዖ። ወሀቦሙ ትእምርተ እንዘ ይብል ዘሰዓምኩ ውእቱ ኪያሁ አኃዙ።
                    ******
፵፰፡ የሚያሲዘው ይሁዳ የምስመው እሱ ነው እሱን ያዙ ብሎ ምልክት ሰጣቸው፡፡
አንድም የሚያሲዝበትን ምልክት ነገራቸው።
                    ******
፵፱፡ ወቀርበ ይእተ ጊዜ ኀበ እግዚእ ኢየሱስ ወሰዓሞ ወይቤሎ በሀ ረቢ።
                    ******
፵፱፡ ወደ ጌታ ቀርቦ መምህር ቢሰኛህን ጥለኛህን አያውለው አያሳድረው ብሎ እጅ ነሳው፡፡
(ሐተታ) ከሱን ሌላ ቢሰኛ ጠበኛ አለው አያውለኝ አያሳድረኝ ሲያሰኘው ነው፡፡
                    ******
፶፡ ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ በእንተ ዝንቱኑ መጻእከ አርክየ።
                    ******
፶፡ ወዳጄ ትእምርተ ፍቅሩን ትእምርተ ጸብእ አድርገኸው መጣህን አለው።
ወእምዝ ቀርቡ ወአንሥኡ እደዊሆሙ ወአሐዝዎ ለእግዚእ ኢየሱስ።
እጃቸውን አንስተው ማለት ጌታን አጽንተው ያዙት።
                    ******
፶፩፡ ወናሁ ተንሥአ እምእለ ምስሌሁ  ለእግዚእ ኢየሱስ ሰፍሐ እዴሁ ወመልሐ መጥባሕቶ ወዘበጦ ለገብረ ሊቀ ካህናት።
                    ******
፶፩፡ ከጌታ ጋራ ካሉት አንዱ ተነሥቶ ሰይፉን መዞ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መታው።
ወመተሮ ዕዝኖ ዘየማን፣
ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው ትፈቅድኑ ንዝብጦሙ ብለውታል በሉቃስ፡፡ አብሮ መብላት አብሮ ለመሞት እንጂ ነው እንበላቸው እንበላቸው ተባብለዋል። እሱ ፈጣን ነውና መታው ቀኝ ጀሮውን ቈረጠው። ከመታው አንገቱን አይለውም ቢሉ የካህን እጅ አያቀናምና ለአንገቱ ያለው ለጆሮው ሆነ።
አንድም አንገቱን ብሎት ቢሆን በሞተ ነበር። የጌታም ሞት ርትዕ በተባለ ነበርና። ጆሮውንሳ ቢሉ በተአምራት ቀጥሎለታል፡፡ ጆሮ የቀጠለ አንገት መቀጠል ይሳነዋልን ብሎ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም፣ ትንቢት ለትትቀረጽ ይእቲ ዕዝን እንተ ኢትሰምዖ ለውእቱ ነቢይ ተብሎ ተነግሯል። ምሳሌም ወለእመ  አጥረይከ ገብረ ዕብራዌ ቅንዮ ስድስተ ዓመተ ወበሳብዕ ዓም አግዕዞ በከንቱ።
ዕብራዊ ባሪያ ቢኖርህ በደመወዝ ገዝተህ በሰባተኛው ዓመት ገንዘብ ሳትሰጥ ነጻ አውጣው ትላለች ኦሪት፡፡ እሱ ግን የጌታዬ ባሕርዩ ተስማምቶኛል። የእመቤቴ እንጀራዋ ወጧ ጣፍጦኛል ነጻ መውጣቱ ይቅርብኝ ያለ እንደሆነ ከቤተ እግዚአብሔር ወስደህ ከመድረኩ አስተኝተህ ጆሮውን ተርትረህ አፍንጫውን ሰቊረህ እስከ ዕለተ ሞቱ ግዛው ትላለች ኦሪት። እንደዚህም ሁሉ በሰባተኛው ሽህ ለዲያብሎስ ከመገዛት ላወጣችሁ መጥቼ ነበር አናምን ካላችሁ በሥጋችሁ ቄሣር በነፍሳችሁ ዲያብሎስ ይሠልጥንባችሁ ለማለት። ያውስ ቢሆን ግራዪቱ አለመሆኑዋ ቀኝቱ መሆኑዋ ስለምን ቢሉ ከነገደ ይሁዳ የተወለዱ ቀኝ ቀኝ አካላቸውን እየተቀቡ መንግሥት ከነገደ ሌዊ የተወለዱ ቀኝ ቀኝ አካላቸውን እየተቀቡ ክህነትን ገንዘብ ያደርጉ ነበር ክህነትንም መንግሥትንም እንዳሳለፈባቸው ለማጠየቅ በቀኝ ጆሮው ምትረትን አዘዘበት።
                    ******
፶፪፡ ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ አግብእ ለመጥባሕትከ ውስተ ቤታ። ዘፍጥ ፱፥፮፡፡ ራዕ ፲፫፥፲፡፡
                    ******
፶፪፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጴጥሮስን ሾተልህን ወደ አፎት ቊጣህን ወደ ትዕግሥት መልስ አለው።
እስመ ኵሎሙ እለ መጥባሕተ ያነሥኡ በመጥባሕት ይመውቱ
በሾተል የገደሉ ሁሉ በሾተል ይሞታሉና።
                    ******
፶፫፡ ይመስለክሙኑ ዘኢይክል አስተብቊዖቶ ለአቡየ ከመ ይፈኑ ሊተ ዘይበዝኁ እም፲ቱ ወ፪ቱ ሠራዊተ መላእክት።
፶፫፡ ከአሥራ ሁለቱ ነገደ መላእክት የሚበዙትን ይልክልኝ ዘንድ አባቴን መለመን መማለድ የማይቻለኝ ይመስላችኋልን
                    ******
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
24/10/2011 ዓ.ም

Saturday, June 29, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 126

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
ምዕራፍ ፳፮።
                    ******        
ዘከመ ከሠተ ሎሙ ለዘያገብዖ።
፳፡ ወምሴተ ከዊኖ ረፈቀ ምስለ ፲ ወ፪ቱ አርዳኢሁ። ማር ፲፪፥፲፯። ሉቃ ፳፪፥፲፱። ሉቃ ፲፫፥፳፩።
                    ******
፳፡ ሲመሽ በመሸ ጊዜ ከአሥራሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋራ ተቀመጠ።
                    ******
፳፩፡ ወእንዘ ይበልዑ ይቤሎሙ አማን እብለክሙ ከመ ፩ዱ እምኔክሙ ያገብአኒ።
                    ******
፳፩፡ ሲበሉ ከእናንተ አንዱ ያስይዘኛል ብሎ አንዲያሲዘኝ በእውነት እነግራችኋለሁ አላቸው።
                    ******
፳፪፡ ወተከዙ ጥቀ፡፡
                    ******
፳፪፡ ፈጽመው አዘኑ፡፡
ወአኃዙ ይበልዎ በበ፩ዱ አነኑ እንጋ እግዚኦ።
እያንድ አንዳቸው አቤቱ የሚያሲዝህ እኔ ነኝ እኔ ነኝ ይባባሉ ጀመር።
                    ******
፳፫፡ ወአውሥአ ወይቤሎሙ ዘያወርድ እዴሁ ምስሌየ ውስተ መጸብሕየ ውእቱ ያገብዓኒ፡፡
                    ******
፳፫፡ ከእኔ ጋራ ወጥ የሚያወጣው እሱ ያስይዘኛል አላቸው።
(ሐተታ) ለልማዱ ጌታ ስድስቱን አቁሞ ስድስቱን አስቀምጦ ይዞ ይበላሉ ይመገባሉ። ዛሬ የተቀመጡ ነገ ይቆማሉ ወጥ የሚያወጣው በተራ ነው ጌታ አያወጣ ይበላል አውጡልኝ አይልም ስድስተኛው ለአምስቱ ለራሱም እያወጣ ይበላል በዚያ ቀን ከተቀመጡት አንዱ ይሁዳ ነበር ወጥ ማውጣትም ተራው የይሁዳ ነበርና እንዲህ አለ።
                    ******
፳፬፡ ወልደ እጓለ እመሕያውሰ የሐውር በከመ ተሠርዓ በእንቲአሁ። መዝ ፵፥፲።
                    ******
፳፬፡ ተጽሕፈ ሲል ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስም ስለእሱ እንደተጻፈ ይሄዳል ማለት ይሞታል።
ወባሕቱ አሌ ሎቱ ለውእቱ ብእሲ ዘያገብዖ ለወልደ እጓለ እመሕያው።
ነገር ግን ምክንያት ሁኖ ለሚያሲዘው ለዚያ ሰው ወዮለት
እምኃየሶ ሶበ ኢተወልደ ለውእቱ ብእሲ።
ባልተወለደ በተሻለው ነበር።
(ሐተታ) እናቱን ይዳፋት ማለት ነው ቢሉ ኢተፈጥረ ሲል ነው ባልተፈጠረ በተሻለው ነበር ኦሪት ዘልደት እንዲል ዘፍጥረት ሲል። ይህስ ፍጠረኝ ብሎ ፈጥሮታልን ቢሉ ቢፈጥረውስ ግዕዛኑን ነሥቶ ፈጥሮታልን።
                    ******
፳፭፡ ወአውሥአ ይሁዳ ዘያገብዖ ወይቤ አነኑ እንጋ ውእቱ ረቢ፡፡
                    ******
፳፭፡ የሚያሲዘው ይሁዳም የሚያሲዝህ እኔ ነኝ አለው ተለይቼ ብቀር ይታወቅብኛል ብሎ
ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ አንተ ትቤ።
አንተ ትላለህ አለው። መሰወር።
አንድም በፈቃዴ የምሞተውን ሞት በግድ አስገድለዋለሁ ትላለህ።
(ታሪክ) ጌታ ሙሴን በግብፃውያን ሞተ በኵር አምጥቼ አወጣችኋለሁ አለው እንዲህማ ከሆነ የእስራኤልስ በኵር ሊሞት አይደለምን አለው፡፡ እንዲህስ እንዳይሆን የሚያዝያ ጨረቃ ሠርቅ ባደረገች በአሥር ቀን ቀንዱ ያልከረከረ ጥፍሩ ያልዘረዘረ ጠጕሩ ያላረረ ዓመት የሆነው ጠቦት ያለው ከመንጋው። የሌለው ገዝታችሁ እስከ ፲፬ት ቀን አስራችሁ በ፲፬ተኛው ቀን ፩ዱን ሰዓት ከ፫ት ከፍላችሁ ፩ዱን እጅ ትታችሁ በ፪ት እጅ ብርሃን ከሌሊቱም ፩ዱን ሰዓት ከ፫ት ከፍላችሁ በአንዱ እጅ ጨለማ ሠዉት። ስትሠዉትም ፯ት አሥር ፲፪ት ሁናችሁ። ያለው ቤተሰቡን ይዞ የሌለው ጎረቤቱን ጠርቶ ፩ድ በግ እንድትጨርሱ ሁናችሁ ደሙን መቃን መድረኩን እርጩት ያን እያየ ሞተ በኵር ይከለከልላችኋል፡፡ ዝግኑን ቅቅሉን ብርንዶውን አትብሉ ጥብሱን ብሉ ኢታትርፉ እስከ ደግደግ እንዲል። አትርፋችሁ አታሳድሩ ከአንዱ ወደ አንዱ አትውሰዱት የበላችሁትን በልታችሁ የተረፋችሁን ከእሳት ጨምሩት ሐምለ ብኂፅ ረብርቡበት ብሎታል በሀገራቸው አራት ነገር ያመጣሉ፡፡ የወይን ቅጥራን የበለስ ቅጥራን የስንዴ ቅጥራን አዞ ከል። በዚያ ወራት የሚበሉት ቂጣ ነውና እንደ አረቄ እንዲበትንላቸው። ስትበሉትም ጫማችሁን አዝባችሁ ዝናራችሁን ታጥቃችሁ ኩፌታችሁን ደፍታችሁ ቦሎታችሁን ይዛችሁ እየቸኮላችሁ ብሉት አጥንቱን አትስበሩት ብሏቸዋል ይህ ሁሉ ምሳሌ ነው። በግዕ የጌታ ምሳሌ ዓመት የሆነው ጠቦት ወርድ እንጂ ቁመት አያክልም። ጌታም ፍጹም የሠላሳ ዓመት ጐልማሳ ሲሆን ነውና የተሰቀለ ዓመት የሆነው ጠቦት ቀንዱ ያልከረከረ ጥፍሩ ያልዘረዘረ ጠጕሩ ያላረረ ማለቱ ምክንያተ ኃጢአት የለበትምና። የሚያዝያ ጨረቃ ሠርቅ ባደረገች በአሥር ዋጅታችሁ እስከ አሥራ አራት አስራችሁ በአሥራ አራት ቀን ሠዉት ማለቱ የጌታም ምክረ ሞቱ በአሥር ተጀምሮ በአሥራ አራተኛው ቀን ተፈጽሟል። በሁለት እጅ ብርሃን በአንድ እጅ ጨለማ ሠዉ ማለቱ ከነግህ እስከ ቀትር ብርሃን ሁኑዋል። ከቀትር እስከ ሰዓት ጨለማ ሁኑዋል። ወጸልመ ኵሉ ዓለም እንዲል። በሠርክ ብርሃን ሁኑዋል። ወፍና ሠርክ ይብርህ እንዲል። ስትሠዉትም ሰባት አሥር አሥራ ሁለት ሁናችሁ ሠዉት ማለቱ ሰባት በእሳቸው ፍጹም ነው አሥርም በእኛ ፍጹም ነው ፍጹማን ሁናችሁ ተቀበሉ ሲል ፲፪ት ማለቱ ለጊዜው የሚቀበሉት አሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል ናቸው ፍጻሜው ግን አሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ናቸውና፡፡ ደሙን መቃን መድረኩን እርጩት ማለቱ ለጊዜው ያን እያየ ቸነፈር ይከለከልላቸዋል። ዛሬም ሥጋውን ደሙን ከሚቀበሉ ምዕመናን አጋንንት ላለመቅረባቸው ምሳሌ። ዝግኑን ቅቅሉን አትብሉ ማለት ሙስና መቃብር አገኘው አትበሉ ሲል ነው። ብርንዶውን አትብሉ ማለቱ ደም ካለ ነፍስ አትለይም። እስመ ነፍስ ተኃድር በደም እንዲል። ነፍስ ያልተለየውን ሥጋውን እንበላለን አትበሉ ሲል። ጥብሱን ብሉ ማለቱ መለኮት የተዋሐደውን ነፍስ የተለየችውን ሥጋውን እንበላለን በሉ ሲል ነው። አታሳድሩ አለ ካሣ ሳይፈጸም አላደረምና ከአንዱ ወደ አንዱ አትውሰዱት አለ ለጊዜው መካነ መስቀሉ ለመካነ መቃብሩ ቅርብ ነው። ፍጻሜው ግን ዛሬም መሥዋዕት ከአንዱ ሠርቶ ወደአንዱ ወስዶ መሠዋት አይገባምና የበላችሁትን በልታችሁ የተረፋችሁን ከእሳት ጨምሩት ማለቱ የተቻላችሁን ያህል ምሥጢር መርምራችሁ የቀረውን መንፈስ ቅዱስ ያውቃል በሉ አትጋፉ ሲል ነው፡፡ እሳት የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ። ሐምለ ብኂዕ ረብርቡበት ማለቱ ለጊዜው በዚያ ወራት የሚበሉት ቂጣ ነበርና እንደ አረቄ አንዲበትንላቸው ነው። ዛሬም ሥጋውን ደሙን መቀበል የሚገባ የበሉት የጠጡት ከሆድ ሲጠፋ ለአፍ ምረት ሲሰማ ነውና። ጫማችሁን አዝባችሁ አለ ምግባረ ወንጌልን ሠርታችሁ፤ ዝናራችሁን ታጥቃችሁ አለ ንጽሕና ይዛችሁ ኩፌታችሁን ደፍታችሁ አለ አክሊለ ሦክን እያሰባችሁ በሎታችሁን ይዛችሁ አለ ነገረ መስቀሉን እያሰባችሁ ሲል ነው፡፡ እየቸኮላችሁ ብሉት ማለቱ ለጊዜው መንገደኞች ናቸው ፍጻሜው ግን ሞት አለብን እያላችሁ ኑሩ ሲል ነው። አረጋዊ መንፈሳዊ። ድርሳን። ዓብድ ውእቱ ዘይሄሊ  ዘእንበለ መቃብሩ እንዲል። አጥንቱን አትስበሩት ማለቱ ለጊዜው ግብፃውያን ሲጐዱ እስራኤል አለመጐዳታቸውን መናገር ነው። ፍጻሜው ግን ኃጥአን ሲጐዱ ጻድቃን ላለመጐዳታቸው ምሳሌ ነው በቁሙም የሁለቱን ወንበዶች ጭንና ጭናቸውን እየሰበሩ ሲያወርዷቸው የእሱን አልሰበሩትምና አጽሞ ኢትስብሩ እንዲል። እንደ አርዮስ ፍጡር በመለኮቱ አትበሉ ሲል ነው። ከዚህም ኦሪትን ሠርቶ አሳልፏታል። ንጉሥ ቀድሞ ሹሞት የነበረውንና ኋላ የሚሾመውን አቅርቦ ያን ወቅሶ ሽሮ ይህን አንዲሾም እሱም ወንጌልን የሚሰራ ነውና፡፡
                    ******
ዘከመ ሠርዓ ኢየሱስ አኩቴተ ቊርባን ።
፳፮፡ ወእንዘ ይበልዑ ነሥአ ኅብስተ እግዚአ ኢየሱስ ባረከ። ፩፡ቆሮ ፲፩፥፳፬፡፡
                    ******
፳፮፡ ሲባሉ ጌታ ዳቦውን አንሥቶ ይዞ ባረከ አከበረ ለወጠ።
ወፈተተ።
ገመሰ ቈረሰ።
አንድም ባረከ ገመሰ ቆረሰ ፈተተ አጠቃቀነ አሥራ ሦስት አደረገ፡፡ ጌዴዎን አሥራ ሦስት ሁኖ ሠውቷልና፤
አንድም በአሥራ ሦስቱ ዕፀወ ዕጣን ምሳሌ፤
አንድም አሥራ ሦስቱን ፀዋትወ መከራ እቀበልላችኋለሁ ሲል
አክሊለ ሦክ፡ ተኰርዖ ርእስ፤ ተጸፍዖ መልታሕት፡ ተወክፎ ምራቅ፡ ሰትየ ሐሞት፣ ተዓሥሮ ድኅሪት፤ ተቀሥፎ ዘባን፤ ርግዘተ ገቦ። ርግዘተ ገቦ ከሞተ በኋላ ነው አይሰማውም ብሎ ፀዊረ መስቀል ኃምስቱ ቅንዋት እግሩን እየራሱ ቸንክረውታል ያሉ እንደሆነ የተመቸ ነው። ደርበው ቸንክረውታል ያሉ እንደሆነ ብሱን ያያል። አንዱን እሱ ተቀብሎታል። ፲፪ን ለሐዋርያት ሰጥቷቸዋል ዝ ሥጋየ ዝ ደምየ ብሏቸዋልና ለማስደፈር ጥዒሞ አጥአሞሙ እንዲል።
አንድም ሳይቀበል አቀብሏቸው ቢሆን ቄሱ አቀብሏቸው ሳይቀበል በወጣ ነበርና። ተቀብሎ ያቀብል ለማለት አብነት ለመሆን
ወወሀቦሙ ለአርዳኢሁ። ወይቤሎሙ ንሥኡ ብልኡ ዝ ውእቱ ሥጋየ።
ነገ በመልዕልተ መስቀል የሚሠዋው ሥጋየ ይህ ነው ብሉ፡፡
                    ******
፳፯፡ ወነሥአ ጽዋዓኒ ወአእኰተ።
                    ******
፳፯፡ ጽዋውንም ይዞ አክብሮ ለውጦ ትኩስ ደም አድርጎ
                    ******
፳፰፡ ወወሀቦሙ እንዘ ይብል ስትዩ እምኔሁ ኵልክሙ ዝ ውእቱ ደምየ ዘሐዲስ ሥርዓት ዘይትከዓው በእንተ ብዙኃን ለኅድገተ ኃጢአት።
                    ******
፳፰፡ እንግዳ ሥርዓት የሚሆን የሐዲስ ርስት የመንግሥተ ሰማያት መጽኛ የሚሆን በተሐድሶ ጸንቶ የሚኖር ስለ ብዙ ሰዎች የሚፈስ ደሜ ይህ ነው ከእሱ ጠጡ ብሎ ሰጣቸው።
(ሐተታ) በከፊል ተናገረው አንድ ሰው ተቀብሎ አይፈጽመውምና። እስከ ዕለተ ምጽአት ሲሰጥ ይኖራልና። ለኅድገተ ኃጢአት
ኃጢአት ሊሠርይ፡፡
                    ******
፳፱፡ ወናሁ እብለክሙ ኢይሰቲ እንከ እምይእዜ እምዝንቱ አፂረ ፍሬ ወይን እስከ እንታክቲ ዕለት አመ እሰትዮ ሐዲሰ ምስሌክሙ በመንግሥተ አቡየ።
                    ******
፳፱፡ በአባቴ መንግሥት ማለት በአባቴ ሥልጣን ታድሼ ተነስቼ ከእናንተ ጋራ በጥብርያዶስ እስከምመጣባት ቀን ድረስ ከዚህ የወይን ፍሬ ጭማቂ አልጠጣም ብየ እነግራችኋለሁ።
                    ******
፴፡ አንቢቦሙ። ማር ፲፬፥፳፮፡፡ ዮሐ ፲፮፥፴፪፡፡ ዘካር ፲፫፥፮።
                    ******
፴፡ በኦሪት የሚደገም አለ ያን ደግመው።
ሰቢሆሙ።
ሥጋውን ደሙን ተቀብለው።
አንድም አንቢቦሙ አቡነ ዘበሰማያት ደግመው ወሰቢሆሙ ነገረ ጰራቅሊጦስን ተጫውተው።
                    ******
፴፩፡ ወፅኡ ውስተ ደብረ ዘይት።
                    ******
፴፩፡ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።
(ሐተታ) ሥጋውን ደሙን በመብል በመጠጥ ያደረገውን በሌላ ያላደረገው ስለምን ቢሉ የቀረው ከብት በአፍአ ይቀራል መብል መጠጥ ከሰውነት ይዋሐዳልና በእውነት እንደ ተዋሐደን ለማጠየቅ።
አንድም  መብል መጠጥ ያፋቅራል እንዳፈቀረን ለማጠየቅ ያውስ ቢሆን በስንዴ በወይን ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምን ቢሉ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም፡፡
ትንቢት እምፍሬ ሥርናይ ወወይን ወቅብዕ በዝኃ። ቀዳሜ ሕይወቱ ለሰብእ እክል ወማይ ወይን ወሥርናይ ለዘኢይሰቲ ወይነ ምንትኑ ሕይወቱ ተብሎ ተነግሯል። ምሳሌም መልከጼዴቅ በስንዴ በወይን ይሠዋ ነበር ትንቢቱን አውቆ አናግሯል ምሳሌውንም እንጂ ባወቀ አስመስሏል። ምሥጢሩ ምንድነው ቢሉ ጌታችን እመቤታችን ሲበሉ የኖሩ ስንዴ ወይን ነበረ ፍጹም ሥጋውን ፍጹም ደሙን እንደሰጠን ለማጠየቅ፡፡
አንድም በመሰለ ነገር ለመስጠት ስንዴ ስብ ሥጋ ይመስላል ወይንም ትኩስ ደም ይመስላልና።
አንድም ስንዴ ልባም ሴት የያዘችው እንደሆነ ነውር የለበትም። ነውር የሌለበት ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል። ወይንም አንድ ጊዜ የጣሉት እንደሆነ ኃይል እየጨመረ ይሄዳል። ኃይል የምትሆን ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል።
ወእምዝ ይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ኵልክሙ ትክህዱኒ በዛቲ ሌሊት።
ከዚህ በኋላ ጌታ በዚች ሌሊት ሁላችሁ ትክዱኛላችሁ አላቸው።
እስመ ይብል መጽሐፍ እቀትሎ ለኖላዊ። ወይዘረዉ አባግዓ መርዔቱ።
መጽሐፍ። ጠባቂ ክርስቶስ ይሞታል የመንጋው በጎች ሐዋርያት ይበተናሉ ብሏልና።
                    ******
፴፪፡ ወእምድኅረ ተንሣእኩ አቀድመክሙ ገሊላ።
                    ******
ወደገሊላ እቀድማችኋለሁ ማለት ከተነሣሁም በኋላ መታየትን በገሊላ እጀምርላችኋለሁ
                    ******
፴፫፡ ወአውሥአ ጴጥሮስ።
                    ******
፴፫፡ ጴጥሮስም መለሰ።
ወይቤሎ ለእመሂ ኵሎሙ ክህዱከ አንሰ ኢይክህደክ ግሙራ።
ሁሉም ቢክዱህ እኔ አልክድህም አለው።
                    ******
፴፬፡ ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ አማን እብለከ ከመ በዛቲ ሌሊት ሥልሰ ትክህደኒ ዘእንበለ ይንቁ ዶርሆ፡፡ ማር ፲፬፥፳፡፡
                    ******
፴፬፡ ጌታም በዚች ሌሊት ይሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ብዬ እንድትክደኝ በእውነት እነግርሀለሁ አለው።
                    ******
፴፭፡ ወይቤሎ ጴጥሮስ እመውትሂ ምስሌከ ወኢይክህደከ። ዮሐ ፲፫፥፴፰። ማር ፲፬፥፴፩፡፡ ሉቃ ፳፪፥፴፫ ።
                    ******
፴፭፡ ጴጥሮስም ከአንተ ጋራ እሞታለሁ ሞትክን ሞት አደርጋለሁ እንጅ አልክድሀም አለው፡፡
ወከማሁ ይቤሉ ኵሎሙ አርዳኢሁ።
ተመክቶ ያስመካቸዋል ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ እንደሱ ከእሱ ጋራ ሞትክን ሞት እናደርጋለን አንክድህም አሉ።
                    ******
ዘከመ ጸለየ ኢየሱስ በጌቴሴማን።
፴፮፡ ወእምዝ ሖረ እግዚእ ኢየሱስ ምስሌሆሙ ውስተ ዓፀደ ወይን ዘስሙ ጌቴሴማን።
፴፮፡ ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን አስከትሎ ጌቴሴማን ከሚባለው ወይን ቦታ ሄደ።
                    ******
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
23/10/2011 ዓ.ም

Friday, June 28, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 125

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
ምዕራፍ ፳፮።
                    ******        
፩፡ ወሶበ ፈጸመ እግዚእ ኢየሱስ ዘንተ ኵሎ ነገረ ይቤሎሙ ለአርዳኢሁ። ተአምሩ ከመ እምድኅረ ሠኑይ መዋዕል ይከውን
ፋሲካ፡፡ ማር ፲፬፥፩፡፡ ሉቃ ፳፪፥፩።
                    ******            
፩፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን አስተምሮ ከፈጸመ በኋላ እስከ ሁለት ቀን ድረስ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁን አላቸው፡፡
(ሐተታ) የሚያስተምረው ረቡዕ ነው ብሎ እስከ የወደቀበት ሐሙስ ነው።
አንድም ድኅረ ክልኤ ይላል ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ የሚያስተምርበት ማክሰኞ ነው ብሎ ድኅሩ ሐሙስ ነው ፋሲካ ከሐሙስ አይወጣም።
ወይእኅዝዎ ለወልደ እጓለ እመሕያው።
ወልደ እጓለ እመሕያውን ይይዙታል ማለት እያዛለሁ።
ወይሰቅልዎ
እሰቀላለሁ።
                    ******     
፫፡ ወእምዝ ተጋብዑ ሊቃነ ካህናት ወሊቃናተ ሕዝብ ውስተ ዓፀደ ሊቀ ካህናት ዘስሙ ቀያፋ።
                    ******     
፫፡ ከዚህ በኋላ የሕዝቡ አለቆችና የካህናቱ አለቆች ቀያፋ ከሚባለው ከካህናቱ አለቃ ቦታ ተሰበሰበቡ።
                    ******     
፬፡ ወተማከሩ ከመ በህብል የአኃዝዎ ለእግዚእ ኢየሱስ ወይቅትልዎ።
                    ******     
፬፡ በሐስት አንድ። በህብል ብለህ አጥብቀህ በድፍረት ይዘው ጌታን ይገሉት ዘንድ መከሩ።
                    ******     
፭፡ ወይቤሉ አኮኬ በበዓል ከመ ኢይትሀወኩ ሕዝብ።
                    ******     
፭፡ ነገር ግን ሕዝቡ እንዳይታወኩ በበዓል አይሁን አሉ።
                    ******     
ዘከመ ረፈቀ ኢየሱስ ለድራር በቢታንያ ወበእንተ ተካይዶቱ ለይሁዳ።
፯፡ ወበጺሖ እግዚእ ኢየሱስ ቢታንያ ቦአ ቤተ ስምዖን ዘለምጽ። ዮሐ ፲፩፥፪፡፡ ፲፪፥፫፡፡ ማር ፲፬፥፫።
                    ******     
፯፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢታንያ በደረሰ ጊዜ ከስምዖን ዘለምጽ ቤት ገባ።
ወመጽአት ኀቤሁ ብእሲት እንተ ባቲ ቢረሌ ዘምሉዕ ዕፍረተ ዘአልባስጥሮስ ዘብዙኅ ሤጡ።
ዋጋው ብዙ የሚሆን የደቀቀ የጣፈጠ ሽቱ ይዛ።
አንድም ዘአልባሰ ጢሮስ ይላል በጢሮሳዊ ግምጃ ዋጋ ልክ በሦስት መቶ ወቄት የተገዛ ሽቱ የያዘች ሴት መጣች።
ወሦጠት ዲበ ርእሱ ለእግዚእ ኢየሱስ እንዘ ይረፍቅ።
ጌታችን ከስምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችበት።
                    ******     
፰፡ ወርእዮሙ አርዳኢሁ አንጐርጐሩ በእንተ ዝንቱ ነገር።
                    ******
፰፡ ደቀ መዛሙርቱ ይህን አይተው አዘኑ።
ወይቤሉ ለምንትኑ ዘመጠነዝ ዕፍረተ አኅጐለት ዛቲ ብእሲት
ይህች ሴት ይህን ያህል ሽቱ ለምን አበላሸች።
እምኢተሠይጠኑ በብዙኅ ንዋይ ይትወሀብ ለነዳያን
ለነዳያን ይመጸወት ዘንድ የሀብዎ ይላል ለነዳያን ይመጸውቱት ዘንድ ለብዙ ዋጋ ባልተሸጠም ነበር አሉ።
                    ******
፲፡ ወአእመሮሙ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎሙ ለምንት ታስርኅዋ ለዛቲ ብአሲት።
                    ******
፲፡ ጌታችን እንዲህ ማለታቸውን አውቆባቸው ይህችን ሴት ለምን ታዳክሟታላችሁ አላቸው፡፡ ሠናየ ግብረ ገብረት ላዕሌየ ሊተ ሲል ለእኔ በጎ ሥራ ሠርታልኛለችና።
                    ******
፲፩፡ ወለነዳያንሰ ዘልፈ ትረክብዎሙ
                    ******
፲፩፡ ነዳያንንስ ዘወትር ታገኝዋቸዋላችሁ
ወጊዜ ፈቀድክሙ ታሤንዩ ሎሙ።
በወደዳችሁ ጊዜ ታደርጉላቸዋላችሁ።
ወኪያየሰ አኮ ዘልፈ ዘትረክቡኒ።
እኔን ግን ዘወትር አታገኙኝም
                    ******
፲፪፡ ወዘንተሰ ዕፍረተ ዘሦጠት ዲበ ርእስየ ለቀበርየ ገብረት።
                    ******
፲፪፡ ይህንም ራሴን የቀባችኝ ሽቱ ለምቀበርበት ቀን አስጠብቃዋለች።
(ሐተታ) ዕለቱን እንዳትቀበው አይሁድ አያስደርሷትም እንደ ሕጋቸው። በሦስተኛው እንዳትቀባው ፈጥኖ ይነሣባታልና። ዛሬም እጸድቅበታለሁ ብሎ ከሠራው በኋላ ማዳከም አይገባም አስቀድሞ ግን ቤተ እግዚአብሔር ልነጽበትን ለነዳያን ልስጣቸውን ብሎ ያማከረ እንደሆነ ሕንጻ እግዚአብሔር ሰው በረኀብ ሲፈርስ ሲበሰብስ ለነዳያን ስጥ እንጂ ማለት ይገባል። ከሠራ በኋላ ግን እንዲህ ማለት አይገባም። ያኑ ከመተው ያደርሰዋልና፡፡
(ታሪክ) አባ ኢዮብ አባ ጴሜን የሚባሉ ፍጹማን መነኮሳት ነበሩ ገባረ ሪፍ የሚባል በዓለም የሚኖር ደግ ሰው ነበረ እየመጣ ይጠይቃቸዋል ሊጠይቃቸው መጥቶ ሳለ አባ ጴሜን አንደምን ሁነህ ትኖራለህ አለው ተክል ተክዬ ራሴን ረድቼ እንግዳ ተቀብዬ በ.ቻለኝ ለነዳያን ተርፌ እኖራለሁ አለው። መልካም ይዘሀል ብሎ አሰናበተው። ከዚህ በኋላ አባ ኢዮብ መጣ ገባረ ሪፍ መጥቶ ነበር አለው ምን ብለህ አሰናበትከው አለው፡፡ እንዲህ ቢለኝ መልካም ይዘኀል አልሁት አለው። መልካም አላደረግህም እኛን መስለሀ ኑር እንዳትለው አለው፡፡ አጥፍቻለሁ ጠርቼ ላምጣው ብሎ ጠርቶ አመጣው፤ እኛን መስለህ ኑር አለው። ከነሁሉም አይቻለኝም ብሏል አባ ኢዮብ አላበጀሁም ማረኝ ብሏል። ይህች ሴት ከራስ ጸጐሯ እስከ እግር ጽፍሯ ይህ ቀራት የማትባል መልከ መልካም ናት፡፡ መላ አካሏን የሚያሳይ መስታወት አላት ልብሷን አኑራ መልኳን አይታ መፍረስ መበስበስ ላይቀር እንዲህ ማማር ምን ይረባል የዚያስ የዚያስ ኃጢአት የሚያስተሠርይ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷል አሉ ለሱ የምቀባው ሽቱ ገዝቼ እሄዳለሁ ብላ በዝሙት የሰበሰበችው ሦስት መቶ ወቄት ወርቅ አላት ይዛ ሄደች። ዲያብሎስ ታመልጠኛለች ይህን ጊዜ ላስታት ብሎ ቀድሞ ከምታውቀው አንዱን መስሎ በአምሳለ ወሬዛ ሠናየ ላህይ ከመንገድ ቆያት። ወዴት ትሄጃለሽ አላት ዝም አለችው አንች ባትነግሪኝ እኔ እነግርሽ የለም እንግዳ ወንድ መጥቶብሽ ለእሱ ልትቀቢው ሽቱ ልትገዥ ትሄሻለሽ አላት አዎን አለችው። ይህም አይደለም ፍቅሩ ያላለቀለት ወንድ መጥቶብሽ ለዚያ የምትቀቢው ሽቱ ልትገዥ ትሄጃለሽ አላት አዎን አለችው ይህም አይደለም በጥቂት ገንዘብ ብዙ ገንዘብ የሚሸጥ ነጋዴ መጥቶብሽ ለእሱ የምትቀቢው ሽቱ ልትገዥ ትሄጃለሽ አላት፤ አዎን አለችው ሁሉንም አዎን አዎን ትያለሽ ማናቸው ነው አላት። እንግዳ ወንድ መጥቶብሽ አልክኝ ከዚህ ዓለም ልዩ የሚሆን ጌታ መጥቷል። ፍቅር ያላለቀለት ወንድ መጥቶብሻል ላልክኝ ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት እንዲል። የሰው ፍቅር አገብሮት ሊሞት መጥቷል፡፡ በጥቂት ገንዘብ ብዙ ገንዘብ የሚሸጥ ባለጸጋ ነጋዴ መጥቶብሻል ላልከኝ አዎን በጥቂት ትሩፋት ብዙ ክብር የሚሰጥ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥተልና ለእሱ የምቀባው ሽቱ ልገዛ እሄዳለሁ ብላ ስሙን ብትጠራበት እንደ ትቢያ በኖ እንደ ጢስ ተኖ ጠፍቶላታል። ከዚህ በኋላ ሃድኖክ የሚባል ባለ ጸጋ ነጋዴ አለ ሄዳ ለነገሥታት የሚገባ ሽቱ አምጣ ብላ ሦስት መቶ ወርቅ ሰጠችው በሀገራቸው ሐሰት የለምና ይህን ያህልስ የሚያወጣ የለኝም አላት እሱ የማያውቀው እናቱ የምታውቀው ዳዊት ሰሎሞን ተቀብተውለት የተረፈ ነበር ከእንዲህ ያለ ቦታ አለ ሽጥላት ብላው ሽጦላት አምጥታ ቀብታዋለች። ይህ ብቻም አይደል ጌታ ግብፅ ሲወርድ ሰሎሜም ፈያታይ ዘየማን ይዘውት ሳለ ከልብሱ ላይ ወዛ ቢያጽቡት ሰፈፈ ይህን በዕቃ አኑረውታል ይህም ተጨምሮበታል።
                    ******
፲፫፡ አማን እብለክሙ በኀበ ሰበክዋ ለዛቲ ወንጌል ይንግሩ ውስተ ኵሉ ዓለም ዘገብረት ዛቲ ብእሲት ተዝካረ ላቲ ወይዝክርዋ።
                    ******
፲፫፡ ወንጌል በተነገረችበት ቦታ ሁሉ ይህች ሴት የሠራችውን ሊነግሩላት ይገባል ብዬ እንዲገባ በእውነት እነግራችኋለሁ። ይኸንም ይዘው አራቱ ሁሉ ጽፈዋታል።
                    ******
፲፬፡ ወእምዝ ሖረ ፩ዱ እም፲ቱ ወ፪ቱ አርዳኢሁ ዘስሙ ይሁዳ አስቆሮታዊ ኀበ ሊቃነ ካህናት፡፡ ማር ፲፬፥፲፡፡ ሉቃ ፳፪፥፫፡፡
                    ******
፲፬፡ ከዚህ በኋላ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮት ሰው የሚሆን ይሁዳ ወደ ሊቃነ ካህናት ሄደ።
(ሐተታ) እንዲያው አይደለም በደብረ ዘይት ሲበሉ። አማን እብለክሙ ከመ ፩ዱ እምኔክሙ ያገብዓኒ አላቸው። ወአነኑ እንጋ እግዚኦ አነኑ እንጋ። የማስይዝህ እኔ ነኝ እኔ ነኝ ይባባሉ ጀመሩ።
(ታሪክ) በደብረ ዘይት ከነበሩ አዕባን አንዱን መጥተህ መስክርበት አለው መጥቶ በይሁዳ ራስ ላይ ሦስት ጊዜ ዙሮ ንጹሕ ደም የምታስፈስስ ይሁዳ ወዮልህ ብሎ መስክሮበታል ዛሬስ አለ አለና ይህ መሠርይ ደንጊያ ያናግርብኝ ጀመር እንኪያስ በማኝ ያግኘኝ ብሎ ወጥቶ ሂዷል።
                    ******
፲፭፡ ወይቤሎሙ ሚመጠነ ትሁቡኒ እመ አገብዖ ለክሙ፡፡
                    ******
፲፭፡ በአስይዛችሁ ምን ያህል ትሰጡኛላችሁ አላቸው።
ወተናገርዎ ምስሌሁ ወተሰነአው ከመ የሃብዎ ፴ ብሩረ።
ሠላሳ ብር እንሰጥሃለን አሉት። ወአስተሐለቁ ነገረ ይላል በሉቃስ፤ ነገር ቆረጡ ነገር አቆሙ ነገር ወሰኑ።
                    ******
፲፮፡ ወእምይእቲ ዕለት አኀዘ ይኅሥሥ ሳሕተ ከመ ያግብዖ ሎሙ፡፡
                    ******
፲፮፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ ከዚያ ቀን ወዲህ ሊያስይዘው ምግላል ቦታ ይሻ ነበር።
                    ******
በእንተ ደኀሪት ድራር።
፲፯፡ ወበቀዳሚት ዕለተ ፍሥሕ መጽኡ አርዳኢሁ ለእግዚእ ኢየሱስ ወይቤልዎ በአይቴ ትፈቅድ ናስተዳሉ ለከ ትብላዕ ፍሥሐ። ማር ፲፬፥፳፪። ሉቃ ፳፥፪-፮።
                    ******
፲፯፡ ፋሲካ ከሚውልባቸው ከ፯ቱ ዕለታት በመጀመሪያዪቱ ቀን።
አንድም ወአመ ቀዳሚት ዕለተ ፍሥሕ ይላል በመጀመሪያዪቱ ፋሲካ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ጌታ ቀርበው በጉን ትበላ ዘንድ በወዴት ልናዘጋጅልህ ትወዳለህ አሉት። ሑሩ ወአስተዳልዉ ዘንበልዕ ፍሥሐ ብሏቸዋል በሉቃስ።
                    ******
፲፰፡ ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ሑሩ ውስተ ሀገር ኀበ እገሌ
                    ******
፲፰፡ ጌታም ወደእገሌ ሀገር ሂዱ አላቸው። እንደ ማርቆስ ምልክት ነግሮ ይሰዳቸዋል።
ወበልዎ ይቤለከ ሊቅ ጊዜየ በጽሐ በኀቤከ እገብር ፋሲካ ምስለ አርዳእየ።
መምህር ከደቀ መዛሙርቴ ጋራ በአንተ ዘንድ በዓል የማከብርበት ቀን ደርሷል አለህ በሉት አላቸው።
                    ******
፲፱፡ ወገብሩ አርዳኢሁ በከመ አዘዞሙ እግዚእ ኢየሱስ።
                    ******
ደቀ መዛሙርቱ ጌታ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡
አስተዳለው ሎቱ ፍሥሐ።
በጉን የሚያርዱበት ወቅለምት ደሙን የሚቀበሉበት ብርት ሥጋውን የሚቀቅሉበት ድስት አዘጋጅተዋል።
                    ******
ዘከመ ከሠተ ሎሙ ለዘያገብዖ።
፳፡ ወምሴተ ከዊኖ ረፈቀ ምስለ ፲ ወ፪ቱ አርዳኢሁ። ማር ፲፪፥፲፯። ሉቃ ፳፪፥፲፱። ሉቃ ፲፫፥፳፩።
፳፡ ሲመሽ በመሸ ጊዜ ከአሥራሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋራ ተቀመጠ።
                    ******
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
21/10/2011 ዓ.ም