Sunday, December 31, 2017

ደብረ ምሕረት የረቦ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
የረቦ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በደጀን ወረዳ ቤተክህነት ሥር የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ቤተክርስቲያኑ ከደጀን ከተማ በምሥራቅ አቅጣጫ ሃያ ሰባት ኪሎሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ወደቦታው ለመሄድ ለሚፈልጉ ሰዎች ከደጀን ከተማ ተነሥተው ጉባያ በሚለው መኪና ገብተው ቦታውን ያለምንም ችግር ማግኘት ይችላሉ፡፡ እንደአሁኑ መኪና ሳይኖር ግን ከሦስት ሰዓት እልህ አስጨራሽ የእግር ጉዞ በኋላ ነበር ቦታው የሚገኘው፡፡ ቦታው ጥንታዊ ቦታ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ሆኖም ግን መዛግብትን ማገላበጥ አባቶችንም መጠየቅ የሚያስፈልገው ጉዳይ ስለሆነ የተመሰረተበትን ቀን እንዴት እንደተመሠረተ ሙሉ ታሪኩን መናገር አልችልም፡፡ እኔም በቦታው ተወልጀ ያደግሁ መሆኑን እንጅ ጥንታዊነቱን ጠይቄም ሆነ መዛግብትን አገላብጨ አላውቅም፡፡ ሆኖም ግን መዛግብትን ማገላበጥ አባቶችን መጠየቅ እንደሚኖርብኝ አውቃለሁ፡፡ ከቤተክርስቲያኑ በታች የሚገኘው ዋሻ ጥንታዊ የቤተክርስቲያኑ መገኛ እንደነበር ይነገራል ሆኖም ግን በመዛግብት እና በአባቶች ማረጋገጫነት መታገዝ ስለሚኖርበት ወደፊት እገልጥላችኋለሁ፡፡

“ቅባት መጠመቅ አለበት” ሊቀ ሊቃውንት ሰሎሞን ዳዊት



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
በመጀመሪያ እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም በፍቅር በአንድነት አደረሳችሁ እያልሁ ከዛሬ ሁለት  ዓመታት በፊት የጻፍኋትን ግጥም እነሆ እላለሁ፡፡ ከዚህ በፊት ያነበበው ሰው ይህንን አልፎ ወደዋናው ርእሰ ጉዳይ መሄድ ይችላል፡፡ መብቱ በሕግ የተፈቀደ ነው ብያለሁ!
                         *********************************
በዱራ ሜዳ ላይ ናቡከደነፆር አምላኩን አቆመው፣
በስድሳ ክንድ ቁመት በስድት ክንድ ወርድ ከወርቅ አቅልጦ ሠራው፡፡
አምላኩን ሊያስመርቅ ያልተመረቀ አምላክ መርቁልኝ ብሎ፣
መኳንንት፣ ሹማምንት፣ አዛዥ፣ አዛውንቱን፣ መጋቢውን ሁሉ ጠራቸው በቶሎ፡፡
የንጉሥ ትዕዛዝ ነው ከታች ባትን ከላይም አንገትን ሊያስቆርጥ የሚችል፣
ታዲያ ማን ይቀራል? ማንስ ይንቀዋል? ማን ያቃልለዋል? READ MORE!
         ****************************************

“ለካስ ጊዜው ኖሯል”



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ድጋሜ እንድለጥፈው ጊዜው አስገደደኝ! ይህንን ጽሑፍ ከዚህ በፊት በራሴ ገጽ ላይ ለጥፌው ነበር፡፡ የዚህን ልጥፍም እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ማግኘት ይቻላል፡፡ http://melkamubeyene.blogspot.com/2015/05/blog-post_98.html ዛሬም መጠነኛ ማሻሻል በማድረግ እነሆ ብያለሁ!
                                 ******************
አንድ ስሙን ለጊዜው የማላስታውሰው ሰው እንዲህ የሚል አባባል አለው “ALL COLOURS WILL AGREE IN THE DARK” ይህን አባባሉን ሳነበው ትልቅ መልእክት እንዳለው ልቤ ተረዳ፡፡ የተረዳው ልቤም መላ አካላቴን አነቃቃው እና አጆቼን ወደ መጻፊያ ሰሌዳው ወሰዳቸው፡፡ በዚያም የሚንኳኳውን የመጻፊያ ሰሌዳ በእኛው በአገራችን በለመድነው ቋንቋ እንዲጽፍ የመጻፊያ ስልቱን ቃኘሁት (ቀየርሁት)፡፡ ከዚያም ይህንን ቁም ነገር በኢትዮጵያዊ ለዛው ተናዘዝሁ፡፡ እነሆ ኑዛዜየን!
                                *********************

Sunday, December 10, 2017

መሠረተ ሐይማኖት ወይስ መሠረተ ክህደት? ክፍል ፲፮--ተፈጸመ



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ዛሬ ከገጽ ፵፯ ጀምረን  እስከ መጨረሻ ገጽ ድረስ ያሉ ስህተቶችን በማስረጃ እንመለከታለን፡፡ በፎቶ ከስር ስለማያይዝላችሁ ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ግን ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ብቻ ነው ትኩረት የማደርገው፡፡
ይህ የመጨረሻየ ክፍል ስለሆነ እስከ ረቡዕ ድረስ ቀስ ብላችሁ ተረጋግታችሁ እንድታነቡት ሰፋ አድርጌ ነው የጻፍሁላችሁ፡፡ ረዘመ እንዳትሉኝ ከወዲሁ እጠይቃለሁ፡፡
********************************

Friday, December 8, 2017

መሠረተ ሐይማኖት ወይስ መሠረተ ክህደት? ክፍል ፲፭



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ዛሬ ከገጽ ፵፪ ጀምረን  ያሉ ስህተቶችን በማስረጃ እንመለከታለን፡፡ በፎቶ ከስር ስለማያይዝላችሁ ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ግን ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ብቻ ነው ትኩረት የማደርገው፡፡
ካሳሁን ምናሉ በዚህ ገጽ ላይ ምእራፍ ዘጠኝን ይጀምራል፡፡ ምእራፉም ስለጌታችን የልደት በዓል ነው የሚናገረው፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ከዚህ በፊት ጥቂት ነገሮችን የተመለከትን ቢሆንም እዚህ ክፍል ላይም በጥልቀት እንመለከታለን፡፡
****************************
ሊቃውንቱ በዚህ ጉዳይ በጥሩ ሁኔታ ያብራሩበት የቪዲዮ ትምህርት አለ ይህንን ሊንክ ጠቅ አድርጉና ተከታተሉት፡፡ ሙሉውን ተከታተሉት እንዳያመልጣችሁ ለሚጠይቋችሁ መልስ ለመስጠት የተዘጋጃችሁ ሁኑ ተብለናል ይህ ደግሞ አንዱ ዝግጅታችን ነው፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=sbriV-ou5NU&feature=youtu.be
***************************

Thursday, December 7, 2017

መሠረተ ሐይማኖት ወይስ መሠረተ ክህደት? ክፍል ፲፬




   ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

የቅባቶቹ መጽሐፍ መሠረተ ሐይማኖት
ዛሬ ከገጽ ፴፪ ጀምረን  ያሉ ስህተቶችን በማስረጃ እንመለከታለን፡፡ በፎቶ ከስር ስለማያይዝላችሁ ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ግን ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ብቻ ነው ትኩረት የማደርገው፡፡
#ረዝሟል_አሳጥረው_እንዳትሉኝ_አደራ_አልቻልሁም፡፡ ምስጢር ከምሥጢር ጋር ሲያያዝ ነውና የሚያምረው ቆራርጨ ማቅረብ አልቻልሁም፡፡ ከዚህ በፊት ቆራርጨ ለወልደ አብ መጽሐፍ ክህደቶች መልስ ስጽፍ አቅርቤው ነበር ሆኖም ግን ምሥጢሩ ከምሥጢሩ ጋር አልተያያዘልንም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሁሉንም በአንድ ማቅረብ ችያለሁ፡፡ “የበረታ ቆሞ የደከመ ተቀምጦ” ብላለች ተአምረ ማርያም እና የበረታ ያንብብ የደከመ #SHARE ያድርግና ጊዜ ሲኖረው ያንብበው፡፡ አንድ ጊዜ ማንበብ ሊደክም ይችላልና፡፡

Monday, December 4, 2017

መሠረተ ሐይማኖት ወይስ መሠረተ ክህደት? ክፍል ፲፫



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ዛሬ ከገጽ ፳፰ ጀምረን  ያሉ ስህተቶችን በማስረጃ እንመለከታለን፡፡ በፎቶ ከስር ስለማያይዝላችሁ ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ግን ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ብቻ ነው ትኩረት የማደርገው፡፡
ከዚህ በተጨማሪም መድሎተ አሚን ላይ በቅባተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ ብለዋል የሚለውን ውሸት መድሎተ አሚንን በፎቶ አስቀምጫለሁ፡፡ ፍትሐ ነገሥቱንም እንዲሁ ለማጣቀሻነት እንድትመለከቱት በፎቶ አያይዠላችኋለሁ፡፡

Friday, December 1, 2017

መሠረተ ሐይማኖት ወይስ መሠረተ ክህደት? ክፍል ፲፪



፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ዛሬ ከገጽ ፳፯ ጀምረን  ያሉ ስህተቶችን በማስረጃ እንመለከታለን፡፡ በፎቶ ከስር ስለማያይዝላችሁ ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ግን ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ብቻ ነው ትኩረት የማደርገው፡፡
ቅዳሜ እና እሁድን ቀስ ብላችሁ አንብቡት በዛ ብላችሁ እንዳትሰለቹ!
ካሳሁን ምናሉ ገጽ ፳፯ ላይ ምዕራፍ ሰባት ብሎ በሚጀምረው የገጹ መጨረሻ ላይ እንዲህ ይላል “መንፈስ ቅዱስን ትቶ ወልድን ብቻ በተዋሕዶ ከበረ ማት እንደንስጥሮስ መንፈስ ቅዱስ ህፀፅ እንደማለት ይቆጠራል ምክንያቱም የባሕርይ አባቱን አብን የባሕርይ ሕይወቱን መንፈስ ቅዱስን ትቶ ወልድን በተዋሕዶ ከበረ ማለት ስተት ነው፡፡ ወልድ በማኅጸነ ማርያም ሲፀነስ በመንፈስ ቅዱስ ሲወለድም በመንፈስ ቅዱስ ቀስ በቀስ ሲያድግም በመንፈስ ቅዱስ ነውና ወልደ አብ ወልደ ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ከበረ ማለት ይገባል” ይላል፡፡ እስካሁን ድረስ ካሳሁን ምናሉ ከመምህራን እግር ስር ቁጭ ብሎ የተማረ ሰው ይመስለኝ ነበር ለካ የኔቢጤ ነው በተባራሪ የሰማውን ብቻ ነው የጻፈው፡፡ በፊደል ግድፈቱም ስንወቅሰው የነበረ በስህተት ነው ለካ፡፡ ምን ይፈረድበታል ነገሩን አላወቀውማ አያያዙ አልገባውማ፡፡