Friday, May 31, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 107

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ምሳሌ ዘዓቀብተ ወይን፡፡
ምዕራፍ ፳።
                    ******     
በእንተ ደቂቀ ዘብዴዎስ።
፳፡ ወእምዝ መጽአት ኀቤሁ እሞሙ ለደቂቀ ዘብዴዎስ ምስለ ደቂቃ፡፡ ማር ፲፥፴፭።
                    ******     
፳፡ ከዚህ በኋላ የዘብዴዎስ ልጆች እናት ማርያም ባውፍልያ ልጆችዋን አስከትላ መጣች።
                        ******     
ወሰገደት ሎቱ እንዘ ትስአል
እየማለደተ ሰገደችለት።
(ሐተታ) እንዲያው አይደለም ኢየሩሳሌም ሊወጣ ሆነ የሹመት ነገር አንድ ጊዜ ከተደላደለ በኋላ ያስቸግራልና ሂደሽ ተናገሪልን ለዘመድሽ ብለዋታል፡፡
ወይቤላ ምንተ ትፈቅዲ እግበር ለኪ።
ምን ላደርግልሽ ትወጃለሽ አላት።
                    ******     
፳፩፡ ወትቤሎ ረሷ ሊተ ከመ ይንበሩ እሉ ደቂቅየ ፩ዱ በየማንከ ወ፩ዱ በፀጋምከ በመንግሥትከ።
                    ******     
፳፩፡ በነገሥህ ጊዜ እኒህ ልጆቼ አንዱ በቀኝህ አንዱ በግራህ እንዲቀመጡ አድርግልኝ ማለት አንዱን ቀኛዝማች አንዱን ግራዝማች በልልኝ አለችው።
                    ******     
፳፪፡ ወአውሥአ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤላ ኢተአምሩ ዘትስእሉ
                    ******     
፳፪፡ የምትለምኑትን አታውቁም ማለት የባለጸጋ ልጅ ኃዘን ቢነግሩት አደን እንዲሉ እሞታለሁ እሰቀላለሁ ብላችሁ ሹመት ሽልማት ትለምናላችሁ አለ፡፡
ትክልኑ ሰትየ ጽዋዕ ዘአነ እሰቲ ወጥምቀተኒ ዘአነ እጠመቅ ትጠመቁኑ።
በዚያውስ ላይ የኔን ጽዋ ትጠጣላችሁ የኔን ጥምቀት ትጠመቃላችሁ ማለት እኔ የምሞተውን ሞት ትሞታላችሁ አላቸው።
(ሐተታ) ጽዋዕ ጥምቀት አለው ሞቱን። ጽዋ በተራ እንደሆነ ሞትም በተራ ነውና፡፡ ጽዋ እንዲያፋቅር ሞቱም ያፋቅራልና ጽዋ ፈጥኖ እንዲጨለጥ ፈጥኖ ተነሥቷልና ወአሕፀረ ዕድሜ ለርእሱ እንዲል። ጥምቀት እንዲያነፃ ሞቱም መንጽሒ ነውና።
ወይቤልዎ እወ ንክል
አዎን ይቻለናል አሉት፡፡
(ሐተታ) ለጌታ የሚያድር ሰው ሞትህን ሞት ሕይወትህን ሕይወት አደርጋለሁ ማለት ልማድ ነውና።
አንድም ለፍቅሩ ይሳሳሉ በፍቅሩ ይናደዳሉና።
                    ******     
፳፫፡ ወይቤሎሙ ጽዋዕየሰ ትሰትዩ ወጥምቀትየኒ ትጠመቁ።
                    ******     
፳፫፡ ጽዋዬን ትጠጣላችሁ ጥምቀቴን ትጠመቃላችሁ ማለት ሞቴንስ ትሞታላችሁ።
ወነቢረሰ በየማንየ ወበፀጋምየ አኮ አነ ዘእሁብ።
በግራና በቀኝ መቀመጥ ግን የምሰጥ እኔ አይደለሁም ማለት ቀኛዝማችነት ግራዝማችነት የምሾም እኔ አይደለሁም፡፡
ዘአንበለ ዘአስተዳለወ ሎሙ አቡየ ዘበሰማያት።
ሰማያዊ አባቴ ላዘጋጀላቸው ለነገሥታት ነው እንጂ።
አእምር ከመ ልዑል ይኴንን መንግሥተ ደቂቀ እጓለ እመሕያው ወዘፈቀደ ይሁብ እስመ ኢይሠየም መኰንን ዘእንበለ እምኀበ እግዚአብሔር ይል የለም ቢሉ አልመጣሁበትም ሲል እንዲህ አለ።
አንድም በቀኝ በግራ ሁነን እንሰቀል ትላላችሁን በቀኝ በግራ መሰቀል ለእናንተ አይደለም ሰማያዊ አባቴ በትንቢት ላዘጋጀላቸው ለፈያታዊ ዘየማን ለፈያታይ ዘፀጋም ነው እንጂ።
አንድም ትክልኑ ብለሀ መልስ። በክብር እንኑር ትላላችሁን እንግዲህስ ወዲህ በክብር መኖር ለእናንተ ብቻ አይደለም ለምዕመናን ሁሉ ነው እንጂ፡፡ ወለዲያቆናትኒ በፀጋሙ እንዲል።
                    ******     
፳፬፡ ወሰሚዖሙ ፲ቱ አንጐርጐሩ ላዕለ ፪ቱ አኃው።
                    ******     
፳፬፡ አሥሩ ይኽን ሰምተው በሁለቱ ወንድማማቾች አዘኑ ዛሬስ ከዚህ አኑረውን ሹመት ይካሰሱብን ጀመር ብለው።
                    ******     
፳፭፡ ወጸውዖሙ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎሙ ኢተአምሩኑ ከመ መኳንንቶሙ ለአሕዛብ ይኴንንዎሙ ወዓበይቶሙ ይቀንይዎሙ።
                    ******     
፳፭፡  ጌታ ጠርቶ አሕዛብን ነገሥታቱ እንዲገዟቸው ሹማምቱ እንዲያዟቸው አታውቁምን አላቸው።
                    ******     
፳፮፡ ወለክሙሰ አኮ ከማሁ።
                    ******     
፳፮፡ ለእናንተ ግን እንዲህ አይደለም።
                    ******     
፳፯፡ ወባሕቱ ዘይፈቅድ እምኔክሙ ይኩን ዓቢየ ይኩንክሙ ገብረ ወዘሂ ይፈቅድ እምኔክሙ ይኩን ሊቀ ይኩንክሙ ላዕከ።
                    ******     
፳፯፡  ከናንተ ወገን ገዢ ሊሆን የወደደ ሰው ተገዢ ይሁናችሁ በላይ ሊሆን የወደደም አገልጋይ ይሁናችሁ እንጂ።
                    ******     
፳፰፡ እስመ ኢመጽአ ወልደ እጓለ እመሕያው ከመ ይትለዓክዎ ዘእንበለ ዳእሙ ከመ ይትለዓክ ወየሀብ ነፍሶ ቤዛ ብዙኃን፡፡
                    ******     
፳፰፡  ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስ ሊያገለግል እንጂ ሊያገለግሉት ቤዛ ሊሆን እንጂ ቤዛ ሊሆኑት አልመጣምና። እንዲህም ባለ ጊዜ ፍቅረ ሢመትን አጥፍቶላቸዋል ሁለቱ እኛ የምንገዛቸው መስሎን ነው እንጂ የማንገዛቸው ከሆነ ሹመት ለምናችን ብለዋል፡፡ አሥሩም የሚገዙን መስሎን ነው እንጂ የማይገዙንማ ከሆነ ቢሾሙ ምንዳችን ብለዋል፡፡
                    ******     
፳፱፡ ወእንዘ ይወጽእ እምኢያሪኮ ተለውዎ ሰብእ ብዙኃን።
                    ******     
፳፱፡ ከኢያረኮ ወጥቶ ሲሄድ ብዙ ሰዎች ተከተሉት።
                    ******     
በእንተ ዕውራን ዘኢያሪሆ።
፴፡ ወናሁ ፪ቱ ዕውራን ይነብሩ ጥቃ ፍኖት።
                    ******     
፴፡ ሁለት ዕውራን እነሆ ከመንገድ በአጠገብ ተቀምጠው ነበር፡፡
ወሰሚዖሙ ከመ እግዚእ ኢየሱስ የኃልፍ ጸርሑ።
ጌታ ሲያልፍ ሰምተው አሰምተው ተናገሩ።
ወይቤልዎ ተሣነሃለነ እግዚኦ ወልደ ዳዊት።
የዳዊት ልጅ አቤቱ እዘንልን አሉት።
                    ******     
፴፩፡  ወሰብእሰ ይጌሥፅዎሙ ከመ ያርምሙ።
                    ******     
፴፩፡ ሰዎች ግን ዝም በሉ ይሏቸው ነበር። ተአምራት ይደረጋል ሰው ይሳባል ወንጌል ትሰፋለች ኦሪት ትጠፋለች ብለው።
ወአዕበዩ ጸሪኃ እንዘ ይብሉ ተሣሃለነ እግዚኦ ወልደ ዳዊት
በዓይን ዋዛ ብለው የዳዊት ልጅ አቤቱ እዘንልን ብለው አሰምተው ተናገሩ።
                    ******     
፴፪፡ ወቆመ እግዚእ ኢየሱስ ወጸውዖሙ
                    ******     
፴፪፡ ለዕውር ርቆ መሄድ አይሆንለትምና ቁሞ ጸራቸው።
ወይቤሎሙ ምንተ ትፈቅዱ እግበር ለክሙ።
ምን ላደርግላላችሁ ትወዳላችሁ አላቸው።
                    ******     
፴፫፡ ወይቤልዎ ከመ ይትከሠታ አዕይንቲነ
                    ******     
፴፫፡ ዕውር ምን ይሻሃል ቢሉት ብርሃን እንዲሉ አቤቱ ዓይናችን ይበራልን ዘንድ እንወዳለን አሉት።
                    ******     
፴፬፡ ወአምሀርዎ ለእግዚእ ኢየሱስ
                    ******     
፴፬፡ ጌታችንን አሳዘኑት።
ወገሠሦሙ አዕይንቲሆሙ።
ዓይናቸውን ዳሰሳቸው።
ወበጊዜሃ ነጸሩ።
በዳሰሳቸውም ጊዜ አዩ።
ወተለውዎ።
ለጊዜው በእግር ተከተሉት ፍጻሜው በግብር መሰሉት ከ፸ አርድዕት ገብተው ተቆጠሩ።
አንድም ወእንዘ ይወፅእ እምኢያሪኮ ብለህ መልስ ከልዕልና ወደ ትሕትና በመጣ ጊዜ ነቢያት በግብር መሰሉት
ወናሁ ፪ቱ ዕውራን ይነብሩ ጥቃ ፍኖት።
ባሕታውያን ከዚህ ዓለም አፍኣ በምትሆን በበረሃ አሉ። ፍኖት ሐተታ አንዳለፈው ምዕ ፭ ቊ ፳፭። ባሕታውያንን ዕውራን አላቸው ከማየት ተከልክለዋልና። ምሥጢር ገና አልተገለጸላቸውምና
ወሰሚዖሙ
ጌታ በጸጋ እንዲገለጥ ምሥጢር እንዲገለጥ አውቀው።
ወይቤልዎ ተሣሃለነ
ምሥጢር ግለጥልን አሉት።
ወሰብእሰ።
አጋንንት ግን ገድላቸውን ያስተዋቸው ዘንድ መከራ ያጸኑባቸው ነበር በማደሪያቸው ሰብእ አላቸው።
ወአዕበዩ ጸሪኃ
የአጋንንትን ፆር ታግሠው አመለከቱ።
ወቆመ
በጸጋ ተገለጠሳቸው።
ወይቤሎሙ
ምን ላደርግላችሁ ትወዳላችሁ አላቸው።
ከመ ይትከሠታ
ምሥጢር ሊገለጥልን እንወዳለን አሉት።
ወገሠሦሙ
ምሥጢር ገለጠላቸው።
ወበጊዜሃ
ያን ጊዜ አወቁ።
ወተለውዎ
ባሕታውያን በግብር መሰሉት።
                    ******     
ዘከመ ቦአ እግዚእ ኢየሱስ ኢየሩሳሌም።
ምዕራፍ ፳፩።
፩፡ ወቀሪቦ ኢየሩሳሌም በጽሐ ቤተ ፋጌ እንተ ገቦ ደብረ ዘይት። ማር ፲፩፥፩። ሉቃ ፲፱፥፩-፱፡፡
፩፡ ወደ ኢየሩሳሌም ሊገባ በቀረበ ጊዜ የደብረ ዘይት አጠገብ ከምትሆን ቤተ ፋጌ ደረሰ።
                    ******   
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
23/09/2011 ዓ.ም

Thursday, May 30, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 106

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ምሳሌ ዘዓቀብተ ወይን፡፡
ምዕራፍ ፳።
                    ******     
፩፡ እስመ ትመስል መንግሥተ ሰማያት ብእሴ በዓለ ቤት ዘወፅአ ነግሃ ይትዓሰብ ገባዕተ ለዓደፀ ወይኑ።
                    ******     
፩፡ መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል ሕገ ወንጌል ተስፋ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ለወይኑ ቦታ ምንደኞችን ሊስማማ ማለዳ የወጣ ባለቤትን ትመስላለችና ቀደምት ወይከውኑ ደኃርተ፤ ደኃርት ይከውኑ ቀደምተ ላለው።
አንድም ትመስላለች እኮን።
                    ******     
፪፡ ወተከሃሎሙ  በበዲናር ለለዕለት።
                    ******     
፪፡ በቀን ድሪም ድረም እሰጣችኋለሁ ብሎ የተስማማቸውን
ወፈነዎሙ ውስተ ዓፀደ ወይኑ ይትቀነዩ።
ወይን ጠብቁ ብሎ ወደ ወይኑ ቦታ የላካቸውን ባለቤት ትመስላለች፡፡
(ሐተታ) ነግህ የተባለ ከተወለዱ ጀምሮ እስከ ሰባት ዓመት ያለው ዘመን ነው፡፡ እስከዚያ ሥርዓት አይሠራባቸውም መምህረ ንስሐ የሚይዙ ጾም የሚጀምሩ ከዚያ በኋላ ነውና።
                    ******     
፫፡ ወወፂኦ ጊዜ ፫ ሰዓት ርእየ ካልዓነ እንዘ ይቀውሙ ውስተ ምሥያጥ ፅሩዓነ፡፡
                    ******     
፫፡ በሦስት ሰዓት ቢወጣ ሌሎችን ሥራ ፈተው አደባባይ ቁመው አገኘ።
                    ******     
፬፡ ወሎሙኒ ይቤሎሙ ሑሩ አንትሙኒ ውስተ ዓፀደ ወይንየ ወተቀነዩ ወዘረትዓኒ እሁበክሙ፡፡
                    ******     
፬፡ እሳቸውንም ከወይኔ ቦታ ሂዳችሁ ወይኔን ጠብቁ የቀናኝን እሰጣችኋለሁ አላቸው። በኋላ የመጣን የቀናኝን እሰጥሃለሁ ማለት ልማድ ነው።
ወእሙንቱ ሖሩ።
እሳቸውም ሔዱ።
                    ******     
፭፡ ወወፂኦ ጊዜ ስሱ ወተሱዓት ሰዓት ገብረ ከማሁ።
                    ******     
፭፡ ዳግመኛም በቀትር በተሠዓት ወጥቶ ሥራ ፈትተው ከአደባባይ ቁመው አገኘ፤ እናንተም ሂዳችሁ ወይኔን ጠብቁ የቀናኝን እሰጣችኋለሁ አላቸው።
                    ******     
፮፡ ወጊዜ አሡሩ ወ፩ ሰዓት ወጺኦ ረከበ ከልዓነ እንዘ ይቀውሙ።
                    ******     
፮፡ በሠርክ ወጥቶ ሌሎችን ሥራ ፈተው ከአደባባይ ቁመው አገኘ።
ወይቤሎሙ ለምንት ቆምክሙ ዝየ ኵሎ ዕለተ ፅሩዓኒክሙ።
ቀኑን ሁሉ ሥራ ፈታችሁ ለምን ቁማችኋል አላቸው። ከዚያው ገብቶ ከተቆጠረ ብሎ ኵሎ ዕለተ አለ።
አንድም ኵሎ ሰዓተ ሲል ነው። አሥራ ሁለቱን ሰዓተ መዓልት ሥራ ፈታችሁ ለምን ቆማችኋል አላቸው።
                    ******     
፯፡ ወይቤልዎ እስመ አልቦ ዘተዓሰበነ።
                    ******     
፯፡ የተስማማን የለምና የተስማማን ባይኖር ነው አሉ።
ወይቤሎ ሑሩ አንትሙኒ ውስተ ዓፀደ ወይንየ ተቀነዩ ወዘረትዓኒ እሁበክሙ።
እናንተም ሂዳችሁ ወይኔን ጠብቁ የቀናኝን እሰጣችኋለሁ አላቸው፡፡ ሠለስት የተባለ ከሰባት ዓመት እስከ ሀያ ዓመት ያለው ዘመን ነው። ቀትር ከሃያ እስከ አርባ ያለው ነው። ተሠዓት ከአርባ እስከ ስሳ ያለው ዘመን ነው። ሠርክ ከስሳ እስከ ሰማንያ ያለው ዘመን ነው፡፡ እስከዚያ ድረስ ሃይማኖት ሳይማሩ ምግባር ሳይሠሩ ኑረው ከዚህ በኋላ በመምራን አድሮ አስተምሮ በቃለ መጻሕናት ገሥፆ ምግባር እንዲሠሩ ሃይማኖት እንዲይዙ ማድረግ ነው።
                    ******     
፰፡ ወሶበ መስየ ይቤሎ በዓለ ዓፀደ ወይን ለመጋቢሁ ጸውዖሙ ለገባዕት ወሀቦሙ ዓስቦሙ
                    ******     
፰፡ ሲመሽ የወይን ባለቤት ሹሙን ጠርቶ ለምንደኞች ዋጋቸውን ስጣቸው አለው።
ወአኃዝ ቅድመ እምቀደምት እስከ ደኃርት።
ከገባዕተ ሠርክ ጀምረህ እስከ ገባዕተ ነግህ ስጥ አለው፤
                    ******     
፱፡ ወመጽኡ እለ አሠርቱ ወ፩ ሰዓት።
                    ******     
፱፡ ገባዕተ ሠርክ መጡ።
ወነሥኡ በበዲናር።
ድሪም ድሪም ሰጣቸው።
                    ******     
፲፡ ወመጽኡ ቀደምት
                    ******     
፲፡ ገባዕተ ነግህ መጡ።
ወመሰሎሙ ዘያበዝኅ ሎሙ ውሂበ።
አብዝቶ የሚሰጣቸው መስሏቸው ነበር።
ወወሀቦሙ ሎሙኒ በበዲናር
ለእሳቸውም ድሪም ድሪም ሰጣቸው።
                    ******     
፲፩፡ ወነሢኦሙ አንጐርጐሩ ላዕሌሁ ለበዓለ ቤት።
                    ******     
፲፩፡ ተቀብለው በባለቤቱ አዘኑበት።
                    ******     
፲፪፡ እንዘ ይብሉ እሉ ደኃርት አሐተ ሰዓተ ተቀንዩ ወአስተዓረይኮሙ ምስሌነ ለእለ ፆርነ ክበዳ ወላህባ ለዕለት ።
                    ******     
፲፪፡ የዕለት ፃሯን ጋሯን ትኩሳቷን ማለት ጧት ጀምረን እስከ
ማታ ስንደክም ከዋልነ ከኛ ጋራ ገባዕተ ሠርክን አስተካከልሃቸው ብለው አዘኑ።
                    ******     
፲፫፡ ወይቤሎ ለ፩ እምኔሆሙ ዓርክየ ኢዓመፅኩከ።
                    ******     
፲፫፡ ከገባዕተ ነግህ አንዱን ወዳጀ አልበደልሁህም አለው፡፡
አኮኑ በበዲናር ተከሃልኩከ
በድሪም ተስማምቼህ አልነበረም።
                    ******     
፲፬፡ ወንሣእ ዘይረክበከ ወሑር።
                    ******     
፲፬፡ የሚገባህን ይዘህ ሂድ አለው።
ወፈቀድኩ ለዝ ደኃራዊ አሀቦ ከማከ።
በኋላ ለመጣው ለዚህ እንዳንተ ልሰጠው ወድጃለሁና።
                    ******     
፲፭፡ ወሚመ ኢይደልወኒኑ ዘፈቀድኩ እግበር በንዋይየ።
                    ******     
፲፭፡ ወይም በገንዘቤ የወደድሁትን ማድረግ አይገባኝምን።
አው ዓንይንከኑ ሐማሚ ውእቱ
ዓይንህ ምቀኛ ናት ማለት አንተስ ምቀኛ ነህን።
ወአንሰ ኄር።
እኔ ግን ቸር ነኝ ማለት ምቀኛ አይደለሁም።
                    ******     
፲፮፡ ከማሁኬ ይከውኑ ደኃርት ቀደምተ ወቀደምት ደኃርተ።
                    ******     
፲፮፡ እንደዚህም ሁሉ ገባዕተ ሠርክ ገባዕተ ነግህን ገባዕተ ነግህ ገባዕተ ሠርክን ይሆናሉ።
እስመ ብዙኃን ጽውዓን ወኅዳጣን ኅሩያን።
ጥቂትም ሁነው ብዙም ሁነው የተጠሩ የተመረጡ ናቸውና ከጠገቡ ላለው ቀደምት ይከውኑ ደኃርተ ወደኃርት ይከውኑ ቀደምተ ላለው አርእስት ስጥ።
አንድም ወሶበ መስየ ብለህ መልስ። ምጽአት በደረሰ ጊዜ አምጻኤ ዓለማት ፈጣሬ ዓለማት አብ መጋቢሁ ወልድን አምጻኤ ዓለማት ፈጣሬ ዓለማት ወልድ መጋቢሁ መልአኩን ምዕመናንን ጠርተህ ከኋለኞች ጀምረህ እስከ ፊተኞች ስጥ አለው።
ወመጽኡ እለ አሠርቱ ወ፩ዱሰዓት።
ኋለኞች መጡ
ወነሥኡ በበዲናር።
እንደ ሥራቸው ሰጣቸው
ወመጽኡ ቀደምት
ፊተኞች መጡ
ወመሰሎሙ በቀዲመ አዝማናት በአብዝኆ ገድላት
የሚያበልጥላቸው መስሏቸው ነበር።
ወወሀቦሙ ሎሙኒ
ለሳቸውም እንደ ሥራቸው ሰጣቸው።
ወነሢኦሙ አንጐርጐሩ
ማዘን የለም ነገሩ የሚያሰኝ ስለሆነ ነው እንጂ፡፡ ዋጋቸውን ተቀብለው ፍርዱን አደነቁ።
እሉ ደኃርት አሐተ ሰዓተ ተቀንዩ
ጥቂት ሰዓት መከራ የተቀበሉ እሊህን ብዙ ዘመን መከራ ከተቀበልን ከኛ ጋራ አስተከከላቸው ብለው አደነቁ።
ወይቤሎ ለ፩ እምኔሆሙ አርክየ።
ከደኃርት ጻድቃን አንዱን ወዳጄ አልበደልሁህም አለው። መፍቀሬ ሰብእ ነውና ዓርክየ ይለዋል፡፡
ወፈቀድኩ ለዝ ደኃራዊ አሀቦ ከማከ ወሚመ ኢይደልወኒኑ እግበር ዘፈቀድኩ በንዋይየ።
እንዲህ ማለት ይህን ተናግሮ ዕንጦንስን ከአስካፍ መቃሪን ከክልዔቲ አንስት አዮጳን ከኖላዊ ትሩፍ በብኑዳን ከፈያታይ መዓንዝር መስደዱን መናገር ነው።
አው ዓይንከኑ ሐማሚ እስመ አነ ኄር
እንዲህ ማለት ገባዕተ ሠርክን ከገባዕተ ነግህ ገባዕተ ነግህን ከገባዕተ ሠርክ ማለት ኋለኞችን ከፊተኞች ፊተኞችን ከኋለኞች ያስተካከለበትን ፍርዱን ከሱ በቀር የሚያውቀው አለ መኖሩን መናገር ነው።
ከማሁኬ
አሁን እንደ ተናገርሁ ገባዕተ ሠርክ ገባዕተ ነግህን ገባዕተ ነግህ ገባዕተ ሠርክን ይሆናሉ።
እስመ ብዙኃን
ብዙም ሁነው ጥቂትም ሁነው የተጠሩ የተመረጡ ናቸውና ቀደምት ይከውኑ ደኃርተ ደኃርት ይከውኑ ቀደምተ ላለው ለላይኛው ስጥ። ም ፲፱ ቊ ፴፡፡
(ሐተታ) ነግህ የተባለ ዘመነ አበው ነው ሠለስት ዘመነ መሳፍንት ቀትር ዘመነ ነገሥት ተሠዓት ዘመነ ካህናት ሠርክ ዘመነ ሥጋዌ ነው።
አንድም ነግህ የተባለ ዘመነ አዳም ሠለስት የተባለ ዘመነ አብርሃም ቀትር ዘመነ ሙሴ ተሠዓት ዘመነ ዳዊት ሠርክ ዘመነ ክርስቶስ፤ቀደምት ይከውኑ ደኃርተ፤ ደኃርት ይከውኑ ቀደምተ አለ። በአቤል ጊዜ የነበሩ በዕለተ ዓርብ ያሉትን በዕለተ ዓርብ ያሉት በአቤል ጊዜ የነበሩትን ይሆናሉ።
አንድም በዓፀደ ነፍስ ያሉት በዓፀደ ሥጋ ያሉትን በዓፀደ ሥጋ ያሉት በዓፀደ ነፍስ ያሉትን ይሆናሉ።
አንድም ነግህ ዘመነ ክርስቶስ ሠለስት ዘመነ ሐዋርያት ቀትር ዘመነ ሰማዕታት ተሠዓት ዘመነ ሊቃውንት ሠርክ ዘመነ መነኮሳት ዘመነ ሐዋርያትና ዘመነ ክርስቶስ አንድ ወገን ነው ብሎ። ወሠለስት ዘመነ ሰማዕታት ቀትር ዘመነ ሊቃውንት ተሰዓት ዘመነ መነኮሳት ሠርክ ዘመነ ደኃርት ጸድቃን በዕለተ ዓርብ ያሉት በዕለተ ምጽአት ያሉትን በዕለተ ምጽአት ያሉት በዕለተ ዓርብ ያሉትን ይሆናሉ።
አንድም ንሕነ ሕያዋን የተባሉት ኢንበጽሖሙ ለምውታን የተባሉትን ኢንበጽሖሙ ለምውታን የተባሉት ንሕነ ሕያዋን የተባሉትን ይሆናሉ።
                    ******     
ትንቢት ሣልሲት ዘሕማማት።
፲፯፡ ወእንዘ የዓርግ ኢየሩሳሌም ነሥኦሙ ለ፲ ወ፪ቱ አርዳኢሁ እንተ ባሕቲቶሙ። ማር ፲፥፴፪፡፡ ሉቃ ፲፰፥፴፩።
                    ******     
፲፯፡ ወደ ኢየሩሳሌም ሲወጣ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን አስከትሏቸው ሄደ።
ወአግኃሶሙ እምፍኖት።
ከመንገድ ፈቀቅ አደረጋቸው
(ሐተታ) ወቀደሞሙ በፍኖት ይላል በማርቆስ፤ በፊት ያሉት በኋላ ነው በኋላ ያሉት በፊት ነው ሲሉ ቀድሟቸው ተገኝቷል እንዲህ ሲሆን እሞታለሁ ይላል ብለውታል።
                    ******     
፲፰፡ ወይቤሎሙ ናሁ ነዓርግ ኢየሩሳሌም።
                    ******     
፲፰፡ ኢየሩሳሌም እወጣለሁ።
ወይእኅዝዎ ለወልደ እጓለ እመ ሕያው።
ወልደ እጓለ እመሕያውን ይይዙታል ማለት እያዛለሁ።
ወያገብዕዎ ኀበ ሊቃናት ወጸሐፍት።
ለሊቃናት ለጸሐፍት አሳልፈው ይሰጡኛል።
ወይኴንንዎ በሞት።
ይሙት በቃ ይፈርዱብኛል።
                    ******     
፲፱፡ ወይሜጥውዎ ለሕዝብ።
                    ******     
፲፱፡ ለሕዝብ አሳልፈው ይሰጡኛል
ወይሳለቁ ላዕሌሁ።
ይዘብቱብኛል፣
ወይቀስፍዎ፣
እገረፋለሁ።
ወይሰቅልዎ ።
እገረፋለሁ።
ወይቀትልዎ።
እሞታለሁ።
ወይትነሣእ በሣልስት ዕለት።
በሦስተኛው ቀን እነሣለሁ አላቸው።
                    ******     
በእንተ ደቂቀ ዘብዴዎስ።
፳፡ ወእምዝ መጽአት ኀቤሁ እሞሙ ለደቂቀ ዘብዴዎስ ምስለ ደቂቃ፡፡ ማር ፲፥፴፭።
፳፡ ከዚህ በኋላ የዘብዴዎስ ልጆች እናት ማርያም ባውፍልያ ልጆችዋን አስከትላ መጣች።
                        ******     
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
22/09/2011 ዓ.ም

Wednesday, May 29, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 105

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ዘተግኅሠ ኢየሱስ እምኢየሩሳሌም።
ምዕራፍ ፲፱፡፡
                    ******     
በእንተ ዘከመ ይደልዎሙ ዕሤት ለእለ ይተልውዎ ለእግዚእ ኢየሱስ።
፳፯፡ ወእምዝ አውሥአ ጴጥሮስ ወይቤሎ ናሁ ንሕነ  ኀደግነ ኵሎ ወተሎናከ ምንተ እንከ ንረክብ።
                        ******     
፳፯፡ ጴጥሮስ መለሰ እኛ ሁሉን ትተን ተከትለንሃል ምን እናገኝ ይሆን አለው፡፡
(ሐተታ) ምን ነበረውና እንዲህ አለ ቢሉ አንድ አህያ አንድ በሬ መረቡን መርከቡን ትቶ ተከትሎታልና፡፡ ይህ ሁሉ አይደለም እከብራለሁ ባይ ልቡናውን ትቶ ተከትሎታልና እንዲህ አለ።
                    ******     
፳፰፡ ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ አንትሙ እለ ተለውክሙኒ አመ ዳግም ልደት አመ ይነብር ወልደ እጓለ እመሕያው ዲበ መንበረ ስብሐቲሁ።
                    ******     
፳፰፡ ሰው በሆንኩ ጊዜ ያመናችሁብኝ እናንተ ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስ በዕርገት በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ በኖረ ጊዜ።
ወአንትሙኒ ትነብሩ ዲበ ፲ወ፪ መናብርት።
በአሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል በመምህርነት ትሾማላችሁ።
ወትኴንኑ ፲ተ ወ ፪ተ ሕዝበ እስራኤል።
አሥራ ሁለቱን ነገደ እስራኤልን ታስተምራላችሁ፡፡
አንድም አመ ይነብር ውስተ ዓለም ሐዲስ ይላል ያመናችሁብኝ እናንተ በዕለተ ምጽአት ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስ በጌትነት በተገኘ ጊዜ በአሥራ ሁለቱ ወንበር ትቀመጣላችሁ በአሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል ትፈርዳላችሁ። ያን ጊዜስ መቀመጥም መፍረድም የለም ዛሬ የፈረዱት ፍርድ የማይነቀፍባቸው ስለሆነ እንዲህ አለ፡፡
                    ******     
ወኵሉ ዘኃደገ አብያተ ወአኃወ ወአኃተ አበ ወእመ ወብእሲተ ወውሉደ ወገራውኃ በእንተ ስምየ ምዕተ ምክዕቢተ ይነሥእ
                    ******     
፳፱፡ በእኔ ስም አምኖ በእኔ ስም ስላመነ አባቱን እናቱን ወንድሙን እኅቱን ሚስቱን ቤቱን ንብረቱን ርስቱን የተወ ሁሉ መቶ ዕፅፍ ያገኛል አለ፡፡
(ሐተታ) መቶ እናት አባት መቶ እኅት ወንድም መቶ ሚስት ያገኛል ማለት አይደለም፡፡ በዚህ ዓለም የአባትነት የእናትነት የወንድምነት የእኅትነት የሚስትነት ሥራ ይሠራለታል ሲል ነው።
ወሕይወተ ዘለዓለም ይወርስ።
በወዲያው የዘለዓለም ሕይወት መንግሥተ ሰማይን ይወርሳል፡፡
                    ******     
፴፡ ወብዙኃን ቀደምት ይከውኑ ደኃርተ ወደኃርት ይከውኑ ቀደምተ። ማቴ ፳፥፲፮፡፡ ማር ፲፥፴፩፡፡ ሉቃ ፲፫፥፴።
                    ******     
፴፡ ኋለኞች ፊተኞችን ፊተኞች ኋለኞችን ይሆናሉ ማለት ቀደምት ጸሐፍት ፈሪሳውያን ደኃርት ሐዋርያትን ይሆናሉ አለ ዐሥራቱን በኵራቱን አጥተው፤ ደኃርት ሐዋርያት ቀደምት ጸሐፍት ፈሪሳውያንን ይሆናሉ አለ አግኝተው፡፡
አንድም ቀደምት ሐዋርያት ደኃርት ሠለስቱ ምዕትን፤ ደኃርት ሠለስቱ ምዕት ቀደምት ሐዋርያትን ይሆናሉ ኋላ በሥራ ያሰፉታል እንጂ በጥምቀት በሚገኘው ክብር አንድ ናቸውና፡፡
                    ******     
በእንተ ምሳሌ ዘዓቀብተ ወይን፡፡
ምዕራፍ ፳።
፩፡ እስመ ትመስል መንግሥተ ሰማያት ብእሴ በዓለ ቤት ዘወፅአ ነግሃ ይትዓሰብ ገባዕተ ለዓደፀ ወይኑ።
                    ******     
፩፡ መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል ሕገ ወንጌል ተስፋ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ለወይኑ ቦታ ምንደኞችን ሊስማማ ማለዳ የወጣ ባለቤትን ትመስላለችና ቀደምት ወይከውኑ ደኃርተ፤ ደኃርት ይከውኑ ቀደምተ ላለው።
አንድም ትመስላለች እኮን።
                        ******     
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
21/09/2011 ዓ.ም

Tuesday, May 28, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 104

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ዘተግኅሠ ኢየሱስ እምኢየሩሳሌም።
ምዕራፍ ፲፱፡፡
                         ******     
፲፬፡ ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ኅድግዎሙ ለእሉ ሕፃናት ኢትክልእዎሙ ይምጽኡ ኀቤየ፡፡ ማቴ ፲፰፥፫።
                    ******     
፲፬፡ ወደእኔ ይመጡ ዘንድ ሕፃናትን ተዋቸው አትከልክሏቸው አለ፡፡
እስመ ለዘከመ እሉ ይእቲ መንግሥተ ሰማያት።
መንግሥተ ሰማያት ወንጌል የምትነገር እንደነዚህ ላሉ ነውና፡፡
አንድም መንግሥተ ሰማያት የምትወርስ እንደነዚህ ላሉ ነውና።
                    ******     
፲፭፡ ወአንበረ እዴሁ ላዕሌሆሙ ወኃለፈ እምህየ።
                    ******     
፲፭፡  እጁን ጭኖ ባርኳዋቸው ከዚያ ኄደ፡፡ እነዚህም ከ፪፻ የሚበዙ ናቸው ከኒህም ከፍጹምነት ያልደረስ ሊቀ ጳጳስነት ጳጳስነት ኤጲስ ቆጶስነት ያልተሾመ የለም፡፡ ከእነዚህም አንዱ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ነው፡፡
                    ******     
በእንተ ወሬዛ ባዕል።
፲፮፡ ወናሁ መጽአ ፩ ብእሲ ወይቤሎ ሊቅ ኄር ምንተ እግበር እምሠናያት ከመ እረስ ሕይወተ ዘለዓለም። ማር ፲፥፲፮፡፡ ሉቃ ፲፰፥፲፰፡፡
                    ******     
፲፮፡ አንድ ሰው መጥቶ መምህር የማታልፍ መንግሥተ ሰማያትን እወርስ ዘንድ ከበጎ ነገር ወገን ምን ላድርግ አለው፡፡
                    ******     
፲፯፡ ወይቤሎ ምንተ ትብለኒ ኄር
                    ******     
፲፯፡ አላመነም ብሎ ሳታምንብኝ ለምን ኄር ትለኛለህ አለው።
አንድም ኄር ብለው ይለኛል ብሎ በተንኮል መጥቷልና የሕሊናውን አውቆበት፡፡ብለው ኄር ይለኛል ብለህ ለምን ኄር ትለኛለህ።
አልቦ ኄር ዘእንበለ ፩ እግዚአብሔር።
ከአንድ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር የለም አለው።
ወእመሰ ትፈቅድ ትባእ ውስተ ሕይወት ዕቀብ ትእዛዛተ።
ወደ ሕይወት ማለት መንግሥተ ሰማያት ትገባ ዘንድ ከወደድህስ ሕግጋትን ጠብቅ። ዘፀ ፳፥፲፫፡ ፲፬፡ ፲፭፡ ፲፮።
                    ******     
፲፰፡ ወይቤሎ አይቴኑ ዕቀብ።
                    ******     
፲፰፡ ማን ማን ልጠብቅ።
ዘአዓቅቦን
የምጠብቃቸው ማን ማን ናቸው አለው።
ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ኢትቅትል ነፍሰ
ጌታም ነፍስ አትግደል።
ኢትዘሙ።
አትሰስን።
ኢትሥርቅ።
አትሥረቅ።
ኢትኩን ስምዓ በሐሰት።
በሐሰት አትመስክር።
                    ******     
፲፱፡ አክብር አባከ ወእመከ።
                    ******     
፲፱፡ አክብር ማለት አባትህን እናትህን እርዳ።
ወአፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ
ባልንጄራህን እንደ ራስህ ውደድ አለው።
                    ******     
ወይቤሎ ወሬዛ ዘንተሰ ኵሎ ዓቀብኩ እምንዕስየ
                    ******     
፳፡ ይህንስ ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄያለሁ።
ምንት እንከ ተርፈኒ።
ምን ቀረኝ
ዘተርፈኒ
የቀረኝ ምንድነው አለው።
ወነጸሮ እግዚእ ኢየሱስ ወአፍቀሮ።
ጌታ አይቶ ወደደው።
                    ******     
፳፩፡ ወይቤሎ አሐቲ ተርፈተከ።
                    ******     
፳፩፡ አንዲት ቀርታሃለች አለው።
እመሰ ፈቀድከ ፍጹመ ከመ ትኩን ሑር ወሢጥ ኵሎ ጥሪተከ ወሀብ ለነዳያን።
ፍጹምነትስ ከወደድህ ሂደህ ገንዘብህን ሁሉ ሽጠህ ለነዳያን ስጥ አለው።
ወታጠሪ መዝገበ ዘበሰማያት
በሰማይ መዝገብ ታገኛለህ ማለት መንግሥተ ሰማያትን ትወርሳለህ።
(ሐተታ) እርድና ከምጽዋት ነገረው ሑር ሢጥ ብሎ እርድና፡፡ ሀብ ብሎ ምጽ ዋትን።
አንድም ነዳያን ላም በሬ ፈረስ በቅሎ ቢሰጧቸው ወጥቶ ወርዶ መሸጥ አይሆንላቸውምና። ዳግመኛ የከብቱን ዋጋ የሚያውቅ ባለቤቱ ነውና። እንዳገኙ እንዳይጥሉት።
ወነዓ ትልወኒ።
ለጊዜው በእግር ተከተለኝ ፍጻሜው በግብር ምሰለኝ አለው፡፡
                    ******     
፳፪፡ ወሰሚዖ ወሬዛ ዘንተ ነገረ ወሖረ እንዘ ይቴክዝ፡፡
                    ******     
፳፪፡ እሱም ይኸን ነገር ሰምቶ እያዘነ ሄደ።
እስመ ብዙኅ ጥሪቱ።
ገንዘቡ ብዙ ነውና። ሢጥ ቢለው ስንቱን ይሸጧል ብሎ፡፡
አንድም እሱን መከተል ሽቶ ነበርና ሑር ቢለው።
አንድም ፍጹምነት ሽቶ ነበርና አሐቲ ተርፈተከ ቢለው።
                    ******     
፳፫፡ ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ አማን እብለክሙ ከመ ባዕል እም ዕፁብ ይበውእ ውስተ መንግሥተ ሰማያት፡፡
                    ******     
፳፫፡ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ባለጸጋ ጨርሶ መጽውቶ በጭንቅ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ብዬ አንዲገባ በእውነት እነግራችኋለሁ አላቸው።
                    ******     
፳፬፡ ወካዕበ ዕብለክሙ ይቀልል ይኅልፍ ገመል እንተ ሰቊረተ መርፍዕ እምባዕል ይባዕ ውስተ መንግሥተ እግዚአብሔር፡፡
                    ******     
፳፬፡ ዳግመኛ ባለጸጋ መንግሥተ ሰማይ ከሚገባ ገመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል ብዬ እነግራችኋለሁ።
(ሐተታ) ባይጻፍ ነው እንጂ በእሱ ጊዜ ተደርጓል። በእሱ ጊዜስ አልተደረገም ደቀ መዝሙሩ ታዴዎስ ያደረገውን መናገር ነው፡፡ ይህን ሲያስተምር ነጋድያን ገመል ጭነው መጡ በቃል ያስተማርኸንን አድርገህ አሳየን አሉት አንጥረኛ ወዳጅ ነበረውና መርፌ ስደድልኝ አለው፡፡ ነገሩን አስቀድሞ ሰምቷልና ቀዳዳውን አስፍቶ ሰደደለት፡፡ ምን ቢሰፋ ገመል ያሳልፋል ያንተንም ዋጋ እግዚአብሔር አያስቀርብህ እንደጥንቱ አድርገህ ስደድልኝ አለው፡፡ እንደጥንቱ አድርጎ ሰደደለት ሦስት ጊዜ እያመላለሰ አሳይቷቸዋል፡፡
አንድም አይሁዳዊ አምኖ ተጠምቆ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ አረማዊ አምኖ ተጠምቆ መንግሥተ ሰማያት ቢገባ ይቀላል ብዬ በእውነት እነግራችኋለሁ፡፡ አይሁዳዊ አያደርገውም አረማዊ ያደርገዋል ማለት ነው።
                    ******     
፳፭፡ ወሰሚዖሙ አርዳኢሁ አንከሩ ጥቀ እንዘ ይብሉ መኑ እንጋ ይክል ድኂነ።
                    ******     
፳፭፡ ደቀ መዛሙርቱ ይኸን ሰምተው ገንዘቡን ሁሉ ጨርሶ መጽውቶ መንግሥተ ሰማያት መግባት ለማን ይቻለዋል ብለው ፈጽመው አደነቁ።
አንድም ተአምራት ማድረግ ለማን ይቻለዋል ብለው አደነቁ።
                    ******     
ወነጸሮሙ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎሙ በኀበ ሰብእ ኢይትከሀል ዝ።
                    ******     
፳፮፡ ጌታ አይቷቸው ተአምራት ማድረግ በሰው ዘንድ አይቻልም
ወበኀበ እግዚአብሔርሰ ኵሉ ይትከሃል።
በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ይህ ሁሉ ይቻላል።
አንድም እግዚአብሔር ባላደረበት ሰው ዘንድ አይቻልም። እግዚአብሔር ባደረበት ሰው ዘንድ ግን ይቻላል።
አንድም ገንዘቡን ጨርሶ መመጽወት እግዚአብሔር ላላደረበት ሰው አይቻልም እግዚአብሔር ላደረበት ሰው ግን ይቻላል።
                    ******     
በእንተ ዘከመ ይደልዎሙ ዕሤት ለእለ ይተልውዎ ለእግዚእ ኢየሱስ።
፳፯፡ ወእምዝ አውሥአ ጴጥሮስ ወይቤሎ ናሁ ንሕነ  ኀደግነ ኵሎ ወተሎናከ ምንተ እንከ ንረክብ።
፳፯፡ ጴጥሮስ መለሰ እኛ ሁሉን ትተን ተከትለንሃል ምን እናገኝ ይሆን አለው፡፡
                        ******     
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
20/09/2011 ዓ.ም

Monday, May 27, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 103

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ዘተግኅሠ ኢየሱስ እምኢየሩሳሌም።
ምዕራፍ ፲፱፡፡
                    ******     
፩፡ ወሶበ ፈጸመ እግዚእ ኢየሱስ ተንሥአ እምገሊላ ወሖረ ወበጽሐ ውስተ ብሔረ ይሁዳ ማዕዶተ ዮርዳኖስ። ማር ፲፥፩፡፡
                    ******     
፩፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ነገር አስተምሮ ከፈጸመ በኋላ ከገሊላ ወጥቶ የዮርዳኖስ ማዶ ወደሚሆን ወደምድረ ይሁዳ ደረሰ።
                        ******     
፪፡ ወተለውዎ አሕዛብ ብዙኃን።
                    ******     
፪፡ ብዙ ሰዎች ተከተሉት።
ወፈወሶሙ በህየ
በዚያም አዳናቸው።
                    ******     
በእንተ ኪዳን ዘኢይትፈታሕ
፫፡ ወመጽኡ ኀቤሁ ፈሪሳውያን ያመክርዎ ወይበልዎ። ማር ፲፥፪
                    ******     
፫፡ ፈሪሳውያን ሊፈትኑት እንዲህ ሊሉት መጡ።
ይከውኖሁ ለብእሲ ኀዲገ ብእሲት በኵሉ ዘአበሰት ሎቱ
ሳትሰስንበት ደረቀች ሰነፈች ብሎ ለሰው ሚስቱን መፍታት ይገባዋልን አሉት።
                    ******     
፬፡ ወአውሥአ
                    ******     
፬፡ መለሰ
ወይቤሎሙ ኢያንበብክሙኑ ዘውስተ ኦሪት ዘከመ ፈጠሮሙ እምትካት ተባዕተ ወአንስተ። ዘፍ ፩፥፳፮።
ጥንቱን አዳምን ወንድ ሔዋንን ሴት አድርጎ እንደፈጠራቸው በኦሪት እንደተጻፈ አልተመለከታችሁም አላቸው፡፡
ብእሴ ወብእሲተ ገብሮሙ
ተባዕተ ያለውን ብእሴ አንስተ ያለውን ብእሲተ አለ።
                    ******     
፭፡ ወይቤ ወበእንተዝ የኃድግ ወእሞ ወይተልዋ ለብእሲቱ፡፡ ዘፍ ፪፥፳፬። ፩፡ቆሮ ፮፥፲፮። ኤፌ ፭፥፴፩፡፡
                    ******     
፭፡ ስለዚህ ነገር ሰው አባት እናቱን ትቶ ሚስቱን ተከትሎ ይሄዳ።
(ሐተታ) ቆላ ብትሆን ቆላ ይወርዳል ደጋ ብትሆን ደጋ ይወጣል።
አንድም እሱ ፈቃድ ቢነሣበት በናቴ ላድርገው አይልም እሷም ፈቃድ ቢነሣባት በአባቴ ላድርገው አትልምና፡፡
አንድም በግብር አንድ ይሆናሉና። ወይታለዋ አባግዓ ቀርሜሎስ እንዲል ይትላጸቃ ሲል።
ወይከውኑ ፪ ሆሙ አሐደ ሥጋ
አንድ አካል ይሆናሉ በግብር፡፡
አንድም ወንዶች ቢወልዱ ያንተ ናቸው ሴቶች ቢወልዱ ያንቺ ናቸው አይባባሉምና።
አንድም እሱን ቢመስሉ ያንተ ይሁኑ አትለውም እሷን ቢመስሉ ያንቸ ይሁኑ አይላትምና።
አንድም በዚህ ዓለም ሳሉ በሕጋቸው ጸንተው አሥራት በኵራት ቀዳምያት አውጥተው እንግዳ ተቀብለው ሥጋውን ደሙን በሚገባ ተቀብለው ቢኖሩ በወዲያውም አንድ ዓለም ወርሰው አንድ ፀሐይ ሞቀው ይኖራሉና።
                    ******     
፮፡ ናሁኬ ኢኮኑ ፪ተ።
                    ******     
፮፡ እነሆ ሁለት አይባሉም።
አላ አሐዱ ሥጋ እሙንቱ።
አንድ አካል ናቸው እንጂ።
ዘእግዚአብሔር አስተጻመረ ሰብእ ኢይፈልጥ።
እግዚአብሔር አንድ ያደረገውን ሰው አይለይም፡፡ አትለይ ሲል ነው።
                    ******     
፯፡ ለምንት እንከ አዘዘ ሙሴ የሀብዋ መጽሐፈ ኅዳጋቲሃ ወይድኃርዋ፡፡ ዘዳ ፳፬፥፩።
                    ******     
፯፡ እንዲህ ከሆነ ሙሴ የምትፈታበትን ነውር የሚናገር ደብዳቤ ሰጥቶ ይፍታት ብሎ ለምን አዘዘን አሉት።
                    ******     
፰፡ ወይቤሎሙ ሙሴሰ አዘዘክሙ በከመ እከየ ልብክሙ ትድኃሩ አንስቲያክሙ ።
                    ******     
፰፡ ሙሴስ እንደ ልቡናችሁ ክፋት ሚስቶቻችሁን ትፈቱ ዘንድ አዘዛችሁ።
ወእምፍጥረትሰ አኮ ከማሁ ዘተገብረ፡፡
ጥንቱን ግን የታዘዘው እንዲህ አይደለም አላቸው።
(ሐተታ) አንዲት ሴት ለአንድ ወንድ አንድ ወንድ ለአንዲት ሴት ነው እንጂ የሞተችበት የሞተባት በፈቲው ፆር የሚናደዱ ሆኑ፡፡ ሙሴ ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት የሞተበት ያግባ ብሎታል፡፡ ሲጠላት ጊዜ ወንዱ ልቧን እያሸ የሚገድላት ሆነ ሴቲቱም መርዝ አጠጥታ ሥራይ አብልታ የምትገድለው ሁናለችና እንዲህ አለ።
                    ******     
፱፡ ወአነሂ እብለክሙ ኵሉ ዘይድኅር ብእሲቶ ዘእንበለ ትዘሙ ለሊሁ ረሰያ ዘማ፡፡ ማቴ ፭፥፴፪። ሉቃ ፲፮፥፲፰።
                    ******     
፱፡ እኔም ሳትሰስንበት ደረቀች ሰነፈች ብሎ ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ ዘማ አሰኛት ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡
ወእንተ ደኃርዋ ዘአውሰበ ዘመወ።
በነውር የተፈታችዪቱንም ያገባ በደለ።
                    ******     
፲፡ ወይቤልዎ አርዳኢሁ እመ ከመዝ ውእቱ ሥርዓተ ብእሲ ወብእሲት ኢርቱዕ አውስቦ።
                    ******     
፲፡ የባልና የሚስት ሥርዓት እንዲህ ከሆነ ማለት ሰነፈች ደረቀች ብሎ መፍታት የማይገባ ከሆነ ሊያገቡ አይገባም አሉት፡፡
                    ******     
፲፩፡ ወይቤሎሙ አኮ ለኵሉ ዘይትከሃል ዝንቱ።
                    ******     
፲፩፡  ይህ ንጽሕ ጠብቆ መኖር ለሁሉ አይቻልም።
ዘእንበለ ለዘተውህቦ።
ሀብተ ንጽሕ ለተሰጠው ግዕዛኑ ለጸናለት አራቱ ባሕርያት ለተስማሙለት ነው እንጂ።
                    ******     
፲፪፡ እስመ ቦ ሕፅዋን እለ ከማሁ ተወልዱ እምከርሠ እሞሙ።
                    ******     
፲፪፡ ከእናታቸው ማኅፀን ጀምሮ ሕፅዋን ሁነው የተወለዱ አሉና፡፡ እንደ አባ ባይሉል ልጆች ሙፃዓ ስንት ብቻ ነበራቸው።
ወቦ ሕፅዋን እለ ሐፀውዎሙ ሰብእ።
ጋላ ሻንቅላ ሕፅዋን ያደረጋቸው አሉና ለኒያ ነው እንጂ
ወቦ ሕፅዋን እለ ሐፀዉ ርእሶሙ በእንተ መንግሥተ ሰማያት።
ከቤተ መንግሥት እንበላለን እንጠጣለን ብለው ሕፅዋን የሆኑ አሉ ለኒያ ነው እንጂ።
(ሐተታ) ይህስ አይደነቅም አህያን አልተዋጋም በሬን አልተራገጠም ብሎ።
እስመ ቦ ሕፅዋን
ከእናታቸው ማኅፀን ሕፅዋን ሁነው የተወለዱ አሉና ለኒያ ነው እንጂ። እለ ኤርምያስ ቀደስኩከ እምከርሠ እምከ እንዲል።
ወቦ እለ ሐፀውዎሙ ሰብእ።
መምራን መክረው አስተምረው ንጹሐን ያደረጓቸው አሉና ለኒያ ነው እንጂ፡፡ ሙሴ ኢያሱን ኤልያስ ኤልሳዕን
ወቦ እለ ሐፀዉ ርእሶሙ በእንተ መንግሥተ ሰማያት።
ባሕርያቸው ደካማ ነውና አይችሉትም ብሎ ነው እንጂ ከሕገ ሥጋ ሕገ ነፍስ ከሕገ እንስሳ ሕገ መላእክት እንዲበልጥ ታውቆ የለም መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን ብለው ንጽሕ ጠብቀው ከሴት ርቀው የሚኖሩ አሉና ለኒያ ነው እንጂ፡፡
ወዘሰ ይክል ተዓግሦ ለይትዓገሥ።
መታገሥ የሚቻለው ማለት ንጽሕ ጠብቄ ከሴት ርቄ እኖራለሁ የሚል ግን ንጽሕ ጠብቆ ከሴት ርቆ ይኑር።
                    ******     
በእንተ ሕፃናት እለ መጽኡ ኀበ ኢየሱስ።
፲፫፡ ወእምዝ አምጽኡ ሎቱ ሕፃናተ ከመ ያንብር እዴሁ ላዕሌሆሙ ወይጸሊ።፡ ማር ፲፥፲፫፡፡ ሉቃ ፲፰፥፲፭።
                    ******     
፲፫፡ ከዚያ በኋላ እጁን ይጭንባቸው ዘንድ ማለት በአንብሮተ እድ ይባርካቸው ዘንድ ሕፃናትን ይዘው መጡ። በኤልሳዕ ልማድ፡፡ ሕፃናት መጥተው ዕርግ በራህ ብለው ዘበቱበት ሁለት ድባት አስነሥቶ ፵፪ ሕፃናት አስፈጀ የነቢየ እግዚአብሔር መርገሙ እንዲህ የጐዳ በረከቱ እንደምን ይጠቅም ብለው እያመጡ የሚያስባርኩ ሁነዋልና በዚያ ልማድ አመጡለት።
ወገሠፅዎሙ አርዳኢሁ ለእለ አምጽእዎሙ።
አባቶቻቸው ያመጧቸው ሕፃናትን ተቆጧቸው ይጠቀጥቁናል ብለው፡፡
አንድም ሕፃናትን ያመጧቸው አባቶቻችውን ተቆጧቸው ትምህርት ያስፈቱናል ብለው።
                    ******     
፲፬፡ ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ኅድግዎሙ ለእሉ ሕፃናት ኢትክልእዎሙ ይምጽኡ ኀቤየ፡፡ ማቴ ፲፰፥፫።
፲፬፡ ወደእኔ ይመጡ ዘንድ ሕፃናትን ተዋቸው አትከልክሏቸው አለ፡፡
                        ******     
  ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
19/09/2011 ዓ.ም