Friday, March 23, 2018

ተአኪያሁ!

  ======= ======= ======= ======= =======

ታኦጎሎስ የተባለው ነባቤ መለኮት ቅዱስ ጎርጎርዮስ ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ብሎ የካደውን ንስጥሮስን ከቊስጥንጥንያ ቤተክርስቲያን ያሳደደበት ድርሳኑ ነው ተአኪያሁ! ትርጓሜውም “የወላዲተ እግዚአብሔር ማርያም ድርሳን” ማለት ነው። በዚህ ድርሳኑም ታላቁ ሊቅ እመ ብርሃን ድንግል ማርያምን እንዲህ ያመሰግናታል፦