Wednesday, December 25, 2019

ምርጫ 2012 እና እኛ!


  ==============
ከዚህ በፊት የምርጫ ካርድ እና እኛ ሆድና ጀርባዎች እንደነበርን ማስታወሱ  አይከፋም፡፡ በተለይ እኔ የምርጫ ካርድ ማውጣትን እንደ ኃጢአት ነበር የምቆጥረው፡፡ በርግጥም ኃጢአት ሆኖ ነበር፡፡ ምክንያቱም ካርዳችን ዋጋዋ ምንም ስላልነበር፡፡ 1997 ዓ.ም ዕድሜዬ ለመምረጥ አልደርስልኝ ቢል መታወቂያየ ላይ ዕድሜየ እንዲሞላ ፍቄ ሰርዤ ነበር ካርድ ያወጣሁ፡፡ ያ ይመስለኛል በተከታታይ ለነበሩ ምርጫዎች ካርድ የሚባል ነገር እንዳላይ ብዬ የመምረጥ መብቴን ከራሴ ላይ እንድገፍ ያደረገኝ፡፡ ዘንድሮ 2012 ዓ.ም በትክክል ምርጫው መካሄድ አለመካሄዱን ባላውቅም መምረጥ ብቻ አይደለም መመረጥም ይኖርብናል ብየ አስባለሁ፡፡
መምረጥ መመረጥ ለሀገር ቅን ከማሰብ የሚመጣ ፍቱን ሃሳብ ነው፡፡ የአንተ ካርድ ቤተ ክርስቲያንን እንድትቃጠል ለማድረግም ላለማድረግም ዋጋ አላት፡፡ የአንተ ካርድ ሀገርህ በሰላም እንድትኖርም እንዳትኖርም የማድረግ ልዩ ኃይል አላት፡፡ የአንተ ካርድ የሕይወትም የሞትም ካርድ ናት፡፡ ያችን ካርድ በእጅህ መያዝ ግድ ይላል፡፡ የክልልም ሆነ የፌዴራል ምክር ቤቶች ውስጥ ካህናት ጠምጥመው ቁጭ ብለው ሳይ ደሜ ይፈላ ነበር፡፡ ለካ ደሜ ይፈላ የነበረው እነርሱ ቢያንስ የአንድን አሕዛብ ወንበር መውረሳቸውን ስላላወቅሁ ነበር፡፡ ለሀገር ሰላም ማምጣት ከተፈለገ ወንበሮች ሁሉ  በጠመጠሙ ካህናት መሞላት አለበት፡፡  እነላሊበላ ንግሥናውን ከቤተ ክህነቱ ጋር ደርበው ሊያስተዳድሩ መነሣት አለባቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የሞት የሽረት ትግል ውስጥ መግባት ግዴታችን የሚሆን ይመስለኛል፡፡ አሁን በርካታ ዕድሎች እጃችን ላይ አሉ እነዚያን እድሎች በሙሉ እንጠቀምባቸው፡፡ ግብጽ፣ ሶሪያ፣ ሕንድ ወዘተ በተጓዙበት እንቅልፍ የበዛበት ጉዞ መሄድ አይገባንም፡፡ እኛ መምራቱንም መመራቱንም ከልክ በላይ እናውቅበታለን፡፡ ስለዚህ ከቀበሌ እስከ ፌዴራል ድረስ ሕዝቡን ሊወክሉ የሚችሉ ሰዎችን በጥንቃቄ እንድንመርጥ ማሳሰብ ግዴታ ነው፡፡ የምርጫ ካርዳችንንም በጊዜው ማውጣት ግዴታችን ይሆናል፡፡ 
 
አባቶቻችን ሞተው ያቆዩንን ታሪካችንን እኛም በደማችን ጽፈን ለሚመጣው ትውልድ ሳይበረዝ ሳይከለስ ማውረስ ይኖርብናል፡፡ ድምጹ ተጽእኖ የሚፈጥር የምክር ቤት አባል ሊኖረን ይገባል፡፡ የገቡትን አንግፋቸው ሊገቡ ያሰቡትን እንደግፋቸው፡፡ እኔ ፖለቲከኛ አይደለሁም፡፡ እንዴት ማሳመን እንደሚቻልም አላውቅም፡፡ ነገር ግን ሀገርን ለማፍረስ ፖለቲካን ሽፋን አድርጎ ከሚመጣ ሰው ለሀገሬ መልካም ነገር አስባለሁ ብየ እገምታለሁ፡፡ ታዲያ ምንም ባልሠራ እንኳ የዚያን ሰው ወንበር መያዜ ትልቅ ነገር እንደሆነ አስባለሁ፡፡ ስለዚህ የተሻለውን የምንመርጥበትና ተሽለን በመገኘትም የምንመረጥበትን ነገር ከወዲሁ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ሌሎች ቀድመውናል ነገር ግን ዕድሉ አለን ተስፋ የሚያስቆርጥ ደረጃ ላይ አይደለንም፡፡ ሠርተን እናሳይ!
ሃይማኖትና ፖለቲካ ለየግል ናቸው በሚል የጅልነት ብሂል ሀገራችንን ለጠላት አሳልፈን ልንሰጣት አይገባም፡፡ ዳዊትም ሰሎሞንም ንጉሦች ነበሩ፡፡ በሀገራችን ቅዱስ ላሊበላም ንጉ ነበር፡፡ ነገር ግን ከቤተ ክህነት ጋር ያጋጫቸው ነገር አልነበረም፡፡ በመልካም ጥበብ መሩ አስተዳደሩ እንጅ፡፡ ንግሥናን ከክህነት ጋር አስተባብሮ መምራትን አስተምረውን አልፈዋልና በግብር በሃይማኖት ልንመስላቸው ይገባል፡፡

No comments:

Post a Comment