Friday, December 7, 2018

ሰንበተ ሰንበታት



=============
ሰንበተ ሰንበታት ማለት ጸሎትን ወደ እግዚአብሔር የሚያሳርጉበት ዕለት ማለት ነው፡፡ በዓመቱ ከሚውሉ ሰንበታት ኹሉ ተለይታ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚሳርጉባ እሁድ ናት፡፡ ይች ዕለትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ለሚመጣባት ሰንበተ ሰንበታት አምሳል ናት፡፡ ሰንበተ ሰንበታት በዓመት ሦስት ጊዜ ይከበራል፡፡ በርካታ የጸሎት ጊዜያት አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ሰንበተ ሰንበታት አንዱ ነው፡፡ የአከባበሩ ሥርዓት  እንደሚከተለው ነው፡፡
.
.
.
ዘመን መለወጫ (ዕለተ ዮሐንስ) ሰኞ ከዋለ ከዚህ ሰኞ ጀምሮ ከሰኞ ውጭ ከዋለ ግን ካለፈው ወይም ከሚመጣው ሰኞ እፈልጋለሁጀመረን 133 ቀናትን እንቆጥራለን ያች 133ኛዋ ዕለት እሁድ ናት፡፡ ይች እሁድ የመጀመሪያዋ ሰንበተ ሰንበታት ትባላለች ማለት ነው፡፡ ከዚህ ጀምረን ሰኞን አንድ ብለን ቀጣይ 133 ቀናትን ስንቆጥር ኹለተኛዋን ሰንበተ ሰንበታት እናገኛለን፡፡ ሦስተኛዋ ሰንበተ ሰንበታት ግን ከኹለተኛዋ ሰንበተ ሰንበተ ሰንበታት ቀጥለን 99 ቀናትን ቆጥረን የምናገኛት እሁድ ናት፡፡ እዚህ ላይ ግን ዕለተ ዮሐንስ መቼ መቼ ሲውል ነው ያለፈውን ሰኞ የምንወስደው መቼ መቼ ሲውልስ ነው የሚመጣውን ሰኞ መነሻ የምናደርገው የሚለውን የሚያብራራልን ካለ እፈልጋለሁ፡፡ የተመለከትኳቸው ውሱን መጸሕፍት በዚህ ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ስላላገኘሁባቸው ነው፡፡ ሰንበተ ሰንበታት ግን የሚውሉት አንዱ በጥር አንዱ በግንቦት አንዱ ደግሞ በጳጉሜን ወር ላይ ነው፡፡
.
.
.
በዚህ መሠረት የዘንድሮውን የ2011 ዓ.ምን ሰንበተ ሰንበታት ለማወቅ ዕለተ ዮሐንስ የዋለበትን ማክሰኞ ያዙና ወደ ኋላ የ133 ቀናት መነሻችንን ሰኞን ያዙ፡፡ መነሻ ቀኑ ጳጉሜን 5 ዕለቱ ሰኑይ ይኾናል ማለት ነው፡፡ ከጳጉሜን 5 ጀምራችሁ 133 ቀናትን ስትቆጥሩ የምታገኙት የመጀመሪያው ሰንበተ ሰንበታትን ይኾናል፡፡ ይህ ቀን ማነው?
.
.
.
ኹለተኛውን ለማግኘት ደግሞ ከመጀመሪያው ሰንበተ ሰንበታት ቀጥለን ከምናገኘው ሰኞ ጀምረን ሌላ 133 ቀናትን ቁጥሩ፡፡ ያ ቀን ማነው እስኪ ሂሳቡን አስሉት?
.
.
.
ሦስተኛውን ሰንበተ ሰንበታ ለማወቅ ደግሞ ኹለተኛው ሰንበተ ሰንበታት ከዋለበት ዕለት ቀጥለን ከምናገኘው ሰኞ ጀምረን 99 ቀናትን ስንቆጥር የምናገኘው ይኾናል፡፡ ቀኑ ማነው አስሉት?
.
.
.
የሰንበተ ሰንበታት አከባበር ይህን የሚመስል ነው፡፡ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ይህ ዕለት በደማቅ ክብረ በዓል የሚከበር ትልቅ በዓል ነው፡፡ የበለጠ ስለ አሰላሉ የምታውቁ ሊቃውንት አስረዱን፡፡ እኔ የማውቀው የሰንበተ ሰንበታት አሰላል ይኼ ነው፡፡ ከዚህ የተለየ ካለ አስረዱን፡፡

















No comments:

Post a Comment