Saturday, May 30, 2015

ባል ማነው?

እባካችሁ ሼር በማድረግ ወገኖቻችንን እንታደግ!!!!

ሁለት “ፍቅረኛሞች” ነበሩ፤ አብዝተው “ይዋደዳሉ”፡፡ ዘመኑ ዛሬ አልነበረም እጅግ ብዙ ዘመናትን አስቆጥሯል፡፡ “ታሪክ ራሱን ይደግማል” አለ አሉ አንድ ፈላስፋ፡፡ ማለቴ ዛሬም ያ ከብዙ ዘመን በፊት የነበረው ዘመን ዛሬ ዘመን ሆኖ እየዘመነ ነው ማለቴ ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ “ፍቅረኛሞችንም” ከዛሬው ዘመን ጋር አብረን እናዘምናቸው እና ዘመኑን አብረውን ይዘምኑ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- እነዚያ ሁለቱ “ፍቅረኛሞች” ፍቅራቸውን ወደ ትዳር ደረጃ ከፍ ለማድረግ ስምምነት ላይ ደረሱ፡፡ ጋብቻቸውን ልዩ በሆነ ሁኔታ ማስረግ ጉጉታቸውና ምኞታቸው ነው፡፡ የመኪና ዘር የሚባል አልቀራቸውም፣ አርቲስት የሚባል ከዘፋኝ እስከ ኮሜዲያን ድረስ ሁሉም ተጠርተዋል፤ የካሜራ ባለሙያ በሙሉ  የስዕል ባለሙያዎችም ሳይቀሩ ተጋብዘዋል፤ የአካባቢው ሰው በሙሉ አደራ ልጆቻችንን እንድተመርቋቸው ተብለዋል፤ የሚታረዱት  ፍሪዳዎች  ከመድለባቸው የተነሣ ጫንቃና ሻኛቸው የማይታወቅ ለቁጥር የሚያስቸግሩ እጅግ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ የሚጠጣው መጠጥ ለባላገሩ ጠጅ፣ ጠላ፣ አረቄ ለከተሜውም ቢራው፣ ለስላሳው ተዘጋቷል፡፡ የሙሽሮቹ ልብስ ታዋቂ በሆኑ “ዲዛይነሮች” የተሠራ በርካታ ጥበብ የፈሰሰበት ነው፡፡ በወርቅ እና በዕንቁ የተጌጠ ካባ ሊደርቡ ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡
እናም ይህንን ሁሉ አድርገው የጋብቻቸውን ቀን ቆረጡ፤ ሁሉም በጉጉት ጠበቀ፡፡ ከሙሽሮቹ ይበልጥ የተጠራው ሰው ቋመጠ፡፡ “ሙሽራን ሊሞቀው ሰርገኛን ልብ ወደቀው” የሚባለው አባባል ባይኖር ኖሮ እነዚህን ሰዎች ሊገልጥ የሚችል አቻ ቃል ባልተገኘ ነበር፡፡ የሆነው ሆነና መቼም ቀኑ መሄዱን ውኃም መፍሰሱን አያቆምምና የሰርጉ ቀን ደረሰ፡፡ ሙሽሮቹ የናፈቁት፣ የተጠሩ ሰዎች በጉጉት የጠበቁት ልዩ ትእይንት የሚታይበት ቀን ደረሰ፡፡ እልል ተባለ፣ ተጨበጨበ፣ ሰርገኛንም ልብ ወደቀው፤ ሙሽራንም ሞቀው፣ ዘለለ ሁሉም በየፊናው የየራሱን ደስታ ገለጸ፡፡ ሁሉም በየቋንቋው ደስታውን ገለጸ “ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ” የሚባለውን “ለሙሽሮች ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ” እያሉ እንደ ሚዳቋ ይዘሉ ገቡ፡፡
እየተጨበጨበ፣ እየተዘለለ፣ ሆ ቀን ወጥቶላት ሁሉም እያላት  ጉዞ ወደ ማዘጋጃቤት፡፡ መዘጋጃ ቤቱ እንዲህ አይነት ሰርግ ሲያስተናግድ የመጀመሪያው አይደለም ለካ፡፡ እኔ በጣም ተገርሜያሁ፤ ከመገረሜም የተነሣ እጄን አፌ ላይ ጭኜ ለብዙ ሰዓታት ራሴን ብቻ እያነጋገርሁ ነበር፡፡ ሙሽሮቹ ወደ መዘጋጃ ቤት ኃላፊው በሚዜዎቻቸው ታጅበው ሄዱ፤ ከባለጉዳዮች መቀመጫ ላይ ተቀምጠውም ቃለ መጠይቁን በሚገባ አድርገው መለሱ፡፡
ኃላፊው ፡ “ሥም” አለ
ሙሽሮቹ፡ “እገሌ እና እገሌ”
ኃላፊው፡  “ዕድሜ”
ሙሽሮቹ “25 እና 27 ዓመት”
ኃላፊው “ጾታ”
ሙሽሮቹ፡ “ወንድ”
ኃላፊው፡ “ባል ማነው?”
ሙሽሮቹ፡ “እኔ ባል፤ እርሱ  ደግሞ ሚስት”
ኃላፊው “መጠይቁን ጨርሻለሁ፤ የጋብቻ የምሥክር ወረቀታችሁን እስከማዘጋጅላችሁ ድረስ ትንሽ ጠብቁኝ” አላቸውና የምሥክር ወረቀታቸውን አዘጋጅቶ ሲሰጣቸው ርችቱ ተተኮሰ፣ መኪኖች ሁሉ አክላሉ፣ ሰው ሁሉ አጨበጨበ፣ በእልልታ አቀለጠው፡፡

ዘመናችን ለካ ዘመነ ሰዶም ነው፡፡ ዛሬ ገና ገባኝ ዓለም ዳግም በንፍር ውኃ እንደማትጠፋ ለኖኅ ቃል ኪዳን የተገባለት ቢሆንም እንኳ ነገ በሌላ መቅሰፍት ምድራችን ሙት ባሕር ልትሆን እንደምትችል  ዛሬ ተረዳሁ፡፡ ዓለም ልትጠፋ ትንሽ የቀራት የመሰለኝ ሁለት ወንዶች ሊጋቡ ሄደው ባል ማነው? ሁለት ሴቶችም ሊጋቡ ሄደው ሚስት ማናት? ተብሎ ከሚጠየቅበት ዘመን መድረሴን ሳስታውስ ነው፡፡ ሴት እና ሴት፤ ወንድና ወንድ ሊጋባ ሄዶ ባል ማነው? ሚስት ማናት? መባል እንዴት ያለ ውርደት ነው? 

No comments:

Post a Comment