Wednesday, January 23, 2019

ለፕሮቴስታንት ወንድሞች እና እህቶች!


++ጥምቀትን ባሰብሁ ጊዜ የተጻፈ++

ኢየሱስ ያድናል የሚለውን ንግግር አብዝታችሁ ስትጠቀሙ አስተውለናል።
ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ "ያመነ የተጠመቀ ይድናል" ማር 16፥16 ብሏል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በዮሐንስ እጅ ተጠምቋል በወንጌል እንደተጻፈው። ማቴ 3ን አንብብ።

ጥያቄየ ኢየሱስ ያመነ የተጠመቀ ይድናል ብሎ እርሱ የተጠመቀ ለመዳን ነው ወይ?

ኢየሱስ ያድናል የምትሉንስ እርሱ ድኖ ያድነናል እያላችሁን ነው ወይ፡፡

በነገራችን ላይ "ኢየሱስ ያድናል" የሚለው ስህተት ነው አላልኩም። በደንብ ነውና የሚያድነን። አያድንም ብለንም ስለማናውቅ ይህን አልተቃወምኩም።

ሊቅ ነኝ የምትል የፕሮቴስታንት አስተማሪ ግን ከላይ የጠየኳቸውን ሁለት ጥያቄዎች ያለምንም ማንዛዛት ያለምንም ወሬ ማብዛት በቀጥታ መልሱልኝ።

No comments:

Post a Comment