Thursday, June 27, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 124
Saturday, June 22, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 123
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ደናግል ጠባባት ወአብዳት፡፡
ምዕራፍ ፳፭።
******
በእንተ ምሳሌ ዘመካልይ።
፲፬፡ እስመ ከመ ብእሲ ዘይነግድ ወጸውአ አግብርቲሁ ወወሀቦሙ ንዋዮ ይትገበሩ ቦቱ። ሉቃ ፲፱፥፲፪፡፡
******
፲፬፡ መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል፣ ሕገ ወንጌል ተስፋ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ብላቴኖችን ጠርቶ ወጥተው ወርደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን የሰጣቸውን ነጋዴን ትመስላለችና ትግሁ። አንድም ትመስላለች እኮን።
******
፲፭፡ ቦ ለዘወሀቦ ፭ተ መክሊተ።
******
፲፭፡ አምስት መክሊትን ለሰጠው ሰው አምስት መክሊት አለው አምስት መክሊትን ለሰጠው ሰው ስጦታ አለው ለሰጠው አምስት መክሊት አለው። አምስት መክሊት የሰጠው ሰው አለ።
ወቦ ለዘወሀቦ ፪ተ መክሊተ።
ሁለት መክሊት የሰጠው ሰው አለ እንዳለፈው በል።
ወቦ ለዘወሀቦ አሐደ መክሊተ፣
አንድ መክሊት የሰጠው ሰው አለ።
ወለለ፩ዱ እምኔሆሙ በአምጣነ ይክሉ።
ከሳቸው ወገን ለአንዱም ለአንዱ እንደሚቻላቸው መጠን።
ወነገደ በጊዜሃ።
ሰጥቷቸው ሄደ።
******
፲፮፡ ወሖረ ዝኩ ዘኃምስ መክሊተ ነሥአ ወተገበረ ቦቱ።
******
፲፮፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ አተረፈ።
ወረብኃ ካልዓተ ፭ተ መካልየ።
አምስት አተረፈ አሥር አደረገ።
******
፲፯፡ ወከማሁ ዘሂ ፪ተ መካልየ ረብኃ ካልዓተ መካልየ
******
፲፯፡ እንደዚህ ሁሉ ሁለት መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ አተረፈ አራት አደረገ።
******
፲፰፡ ወዘአሐደሰ መክሊተ ነሥአ ሖረ ወኃለፈ ወከረየ ምድረ ወኃብአ ወርቀ እግዚኡ።
******
፲፰፡ አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ሌባ ቢሠርቀኝ ወንበዴ ቢቀማኝ ቀጣፊ ቢያታልለኝ ብሎ ፈርቶ ሄዶ ምድር ቆፍሮ የጌታውን ወርቅ ቀበረ።
******
፲፱፡ ወእምድኅረ ብዙኅ መዋዕል አተወ እግዚኦሙ ለእሉ አግብርት።
******
፲፱፡ ከብዙ ዘመን በኋላ የነዚያ የባሮች ጌታቸው መጣ።
ወአኀዘ ይትሐሰቦሙ።
ተቈጣጠራቸው።
******
፳፡ ወቀርበ ዘኃምስ መካልየ ነሥአ ወአምጽአ ካልዓተ ኃምሰ መካልየ።
******
፳፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ ያተረፈውን አምስቱን ደርቦ አመጣ።
እንዘ ይብል እግዚኦ ኃምሰ መካልየ ወሀብከኒ።
አቤቱ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር።
አንድም ዘወሀብከኒ የሰጠኸኝ። አምስት መክሊት ነበር።
አኮሁ ኃምስ መካልየ ወሀብከኒ
አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ አልነበረምን።
አንድም ዘወሀብከኒ የሰጠኸኝ አምስት አልነበረምን።
ወናሁ ኃምስ መካልይ ዘረባሕኩ ዲቤሆን።
እነሆ ወጥቼ ወርጄ አምስት አትርፌአለሁ አሥር አድርጌአለሁ አለው።
******
፳፩፡ ወይቤሎ እግዚኡ ኦ ገብር ኄር ወምዕመን ዘበኅዳጥ ምዕመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሰይመከ።
******
፳፩፡ አንተ በጎ ባሪያ በጥቂቱ ከታመንክ በብዙው እሾምሀለሁ።
ባዕ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእከ።
ጌታህ ተድላ ከሚያደርግበት ግባ ማለት ተሾም ተሸለም አለው።
******
፳፪፡ ወመጽአ ዘ፪ተ መክሏተ ነሥአ
******
፳፪፡ ሁለት መክሊት የተቀበለውም መጣ።
ወይቤ እግዚኦ አኮሁ ፪ተ መካልየ ወሀብከኒ።
አቤቱ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ አልነበረምን።
ወናሁ ፪ተ ካልዓተ መካልየ ረባሕኩ
እነሆ ወጥቼ ወርጄ ሁለት አተረፍኩ አራት አደረግሁ አለው።
******
፳፫፡ ወይቤሎ እግዚኡ ኦ ገብር ኄር ወምዕመን ዘበውኍድ ምዕመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሠይመከ ባዕ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእከ።
******
፳፫፡ አንተ በጎ ባሪያ በጥቂቱ ከታመንክ በብዙ ወገን እሾምሀለሁ ጌታህ ተድላ ከሚያደርግበት ግባ ማለት ተሾም ተሸለም አለው።
******
፳፬፡ ወመጽአ ዘሂ ዘ፩ደኒ መክሊተ ነሥአ።
******
፳፬፡ አንድ መክሊት የተቀበለውም መጣ።
ወይቤ እግዚኦ አአምረከ ከመ ብእሲ ድሩክ አንተ ተአርር ዘኢዘራእክ ወታስተጋብዕ ዘኢዘረውከ፡፡
አቤቱ ያልዘራኸውን የምታጭድ ያልበተንኸውን የምትሰበስብ ትነሥእ ዘኢያንበርከ ይላል በሉቃስ ያላኖርኸውን የምታነሳ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና።
******
፳፭፡ ወፈሪህየ ሖርኩ ወከረይኩ ምድረ ወደፈንኩ መክሊተከ ውስተ ምድር።
******
፳፭፡ ሌባ ቢሠርቀኝ ወምበዴ ቢቀማኝ ቀጣፊ ቢያታልለኝ ብዬ ፈርቼ ምድር ቆፍሬ ቀብሬ አኑሬአለሁ። ጠብለልክዋ ውስተ ሰበንየ ይላል በሉቃስ። በመጠምጠሚያዬ ቋጥሬ ይዣለሁ።
ናሁ ንሣእ ንዋየከ።
እነሆ ገንዘብክን ተቀበለኝ አለው።
ወአውሥአ እግዚኡ።
ጌታው መለሰ።
******
፳፮፡ ወይቤሎ ኦ እኩይ ገብር ወሀካይ ተአምረኒኑ ከመ ብእሲ ድሩከ አነ አዓርር ዘኢዘራዕኩ ወአስተጋብዕ ዘኢዘረውኩ።
******
፳፮፡ ያልዘራሁትን የማጭድ ያልበተንሁትን የምሰበስብ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን።
******
፳፯፡ ወእምደለወከ ተግብዕ ወርቅየ ውስተ ማዕድየ።
******
፳፯፡ ይኸን ከአወቅህ ገንዘቤን ልትሰጠኝ የተገባህ ነበር።
ወመጺአየ አነ ለልየ እምአስተገበርክዎ በርዴ።
ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍልኝ በሰጠሁት ነበር።
አንድም እኔ ወጥቼ ወርጄ ባተረፍኩበት ነበር፡፡
******
፳፰፡ ወይቤሎሙ ለእለ ይቀውሙ ህየ ንሥኡ እምኔሁ ዘንተ መክሊተ ወሀብዎ ለዘቦ ፲ቱ መክሊት። ማቴ ፲፫፥፲፪፡፡ ማር ፬፥፳፭፡፡ ሉቃ ፰፥፲፰፡፡ ፲፱፥፳፮፡፡
******
፳፰፡ ይህን መክሊት ከሱ ተቀብላችሁ አሥር መክሊት ላለው
ስጡት።
******
፳፱፡ እስመ ለዘቦ ይሁብዎ።
******
፳፱፡ ላለው ይሰጡታልና ማለት አምስት ላለው አምስት ይሰጡታልና።
ወይዌስክዎ።
ይደርቡለታል አለ አንዱን።
ወለዘለሰ አልቦ ዘሂ ቦ የሀይድዎ።
የሌለውን ግን ያኑ ያለውን ቅሉ ይወስዱበታልና ንሥኡ።
******
፴፡ ወለገብርሰ እኩይ ወሀካይ አውፅእዎ አፍአ ወደይዎ ውስተ ጽልመት ጸናፊ ኃበ ሀሎ ብካይ ወሐቅየ ስነን።
******
፴፡ ያን ሐኬተኛ ባሪያ ግን ልቅሶ ጥርስ ቁርጥማት ወዳለበት ወደጽኑ ጨለማ አግዙት አለ።
አንድም። ቦ ለዘወሀቦ ፭ተ መክሊተ ብለሀ መልስ። ባለ፭ት የተባለ ፍጹም ትምህርት ተምሮ መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ነው፡፡ ባለሁለት የተባለ ፍጹም ትምህርት ተምር መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ነው፤ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን፤ ጳውሎስ ጢሞቴዎስን እንዳወጡ፡፡ ባለአንድ የተባለ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ ነው።
ወሖረ ዝኩ ዘኃምስ መክሊተ ነሥአ፡፡
ፍጹም ትምህርት የተማረው ወጥቶ ወርዶ መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ አወጣ።
ወዘ፩ደሰ መክሊተ ነሥአ፤
ባለአንድ ዓላውያን እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብሎ ፈርቶ ሃይማኖቱን በልቡ የያዘ።
ወይቤሎ አአምረከ ከመ ብእሲ ድሩክ አንተ፡፡
ሕግ ሳትሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ መምህር ሳትሰጥ በስነ ፍጥረት ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብለህ የምትፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና፡፡ አላውያን እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብዬ ፈርቼ
ደፈንኩ ውስተ ምድር
በልቡናዬ ይዣዋለሁ።
ጠብለልክዋ ውስተ ሰበንየ ባለው በአእምሮዬ ጠብቄ አለሁ አለ።
ገብር ሐካይ ተአምረኒኑ።
ሕግ ሳልሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ መምህር ሳልሰጥ በስነ ፍጥረት ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብዬ የምፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን።
ወእምደለወከ።
እንዲህስ ካወቅህ ሹመትክን ልታበረክተኝ ይገባኝ ነበር።
ለልየ እምአስተገበርክዎ።
ወጥቶ ወርዶ ለሚያስተምር በሰጠሁት ነበር።
አንድም ከሁለት ከሦስት ጆሮ ባደረስከው እኔ ተራድቼ ባሰፋፋሁት ነበር፡፡
ንሥኡ እምኔሁ
የእሱን መምህርነት ነሥታችሁ ለዚያ ደርቡለት።
ወለገብርሰ እኩይ አውፅአዎ፡፡
እሱን ግን አውጡት አለ። ከመንግሥተ ሰማይ አይወጣም በመምሕርነት መግባት ቢቀርበት በሕዝባዊነት ይገባል።
(ታሪክ) ይህም በአባ መልክአ ክርስቶስ ታውቋል፡፡ ፍጹም ትምህርት ሳያስተምሩ ቀርተዋል በተባሕትዎ ፈጽመውታል በሚሞቱበት መልአክ ገሰጻቸው ቀለሙ አካል እየገዛ ሲወጣ ታይቷል።
አንድም ባለአምስት ሙሴ ነው አምስቱ መጻሕፍት አሉትና። ባለሁለት ቅዱስ ጴጥሮስ። እንዲህ ግን ስለሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ይበልጣል ሁለት የተባሉ ብሉይና ሐዲስ ናቸውና። ባለአንድ ይሁዳ አውፅእዎ አሁን የተመቸ።
አንድም ባለአምስት ሊቀ ጳጳሳት አንብሮተ እድ ላዕለ ጳጳስ፣ ሰይመ ቀሲስ፣ ሠይመ ዲያቆን፣ ማጥመቅ፣ ማቊረብ። ባለሁለት ቄስ ማጥመቅ፣ ማቊረብ፤ ባለአንድ ዲያቆን ተልእኮ።
አንድም ባለአምስት አሚን፣ ፍሥሐ፣ ምሕረት፣ ትእግሥት ተስፋ፡፡ ባለሁለት አሚን፣ ፍሥሐ፤ ባለአንድ አሚን፡፡
አንድም ባለአምስት ጥምቀት፣ ተአምኖ ኃጢአት፣ ከዊነ ሰማዕት፣ ተባሕትዎ፣ ምንኩስና፤ ባለሁ.ለት ጥምቀት፣ ተአምኖ ኃጢአት፤ ባለአንድ ጥምቀት።
አንድም ባለአምስት ፍጹም ባለጸጋ፤ ባለሁለት እንደ መጠኑ ባለጸጋ፤ ባለአንድ ፍጹም ድኃ።
******
በእንተ ኅልቀተ ዓለም።
፴፩፡ ወአመ ይመጽእ ወልደ እጓለ እመሕያው በስብሐቲሁ ወኵሎሙ መላእክቲሁ ቅዱሳን ምስሌሁ።
******
፴፩፡ የቀደሙ መምሕራን ትመስልን ለምዕመናን መክሊትን ለመምሕራን ወአመ ይመጽእን ለባለጸነች ሰጥተው ይተረጕሙ ነበር። ዛሬ ሁሉም በሁሉ አሉ ብሎ ትመስልን ለምዕመናን ለመምሕራን ለባለጸጎች መክሊትን ለምዕመናን ለመምሕራን ለባለጸጎች። ወአመ ይመጽእን ለምዕመናን ለመምሕራን ለባለጸጎች ሰጥተው ይተረጕማሉ። ወልደ እጓለ እመሕያው መላእክትን አስከትሎ በጌትነት በመጣ ጊዜ።
አሜሃ ይነብር ዲበ መንበረ ስብሐቲሁ።
በሚመሰገን ዙፋን ማለት በጌትነት ይገኛል።
******
፴፪፡ ወይትጋብዑ ኵሎሙ አሕዛብ ቅድሜሁ።
፴፪፡ ሙታን ሁሉ ከሱ ዘንድ ይሰበሰባሉ።
******
ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
15/10/2011 ዓ.ም
Friday, June 21, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 122
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ደናግል ጠባባት ወአብዳት፡፡
ምዕራፍ ፳፭።
******
፩፡ አሜሃ ትመስል መንግሥተ ሰማያት አሥሮን ደናግለ እለ ነሥአ መኃትዊሆን ወወፅአ ውስተ ቀበላ መርዓዊ
******
፩፡ አብነት አሜሃ ይእተ አሚረ ይላል ያን ጊዜ መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል። ሕገ ወንጌል ተስፋ፡፡ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ፋና ይዘው አሥሩ ደናግል ሊቀበሉት የወጡ ሙሽራን ትመስላለች።
አንድም መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል ትመስል መኃትወ ፤ መርዓዊን ሲቀበሉ ፲ ደናግል ይዘውት የወጡ ፋናን ትመስላለች።
አንድም መንግሥተ ሰማይ ምዕመናን ትመስል አሥሮን ደናግለ። ሙሽራውን ለመቀበል ፋና ይዘው የወጡ ደናግልን ትመስላለች፡፡
(ሐተታ) ደናግል አላቸው ምዕመናንን፤ ድንግል በአባት በእናቷ ቤት ሳለች ኋላ ከባሏ ጋራ አንድ የምትሆንበትን ሥራ ስትማር እንድታድግ ምዕመናንም በዚህ ዓለም ሳሉ ኋላ ከክርስቶስ ጋራ አንድ የሚሆኑበትን ሥራ ሲሠሩ ይኖራሉ።
አንድም በተፈጥሮ ደናግል ናቸውና።
አንድም ድንግልና ሥጋ አላቸውና ይሀህ ለሁሉ አይቻልም ብሎ ድንግልና ነፍስ አላቸውና።
******
፪፡ ወኃምስ እምኔሆን አብዳት እማንቱ።
******
፪፡ ከአሥሩ አምስቱ ሰነፎች ናቸው፡፡
ወኃምስ ጠባባት ።
አምስቱ ልባሞች ናቸው።
******
፫፡ ወዓብዳትሰ ነሢኦን መኃትዊሆን ኢነሥኣ ቅብዓ ምስሌሆን።
******
፫፡ ሰነፎች ፋና ይዘው በማሠሯቸው ዘይት አልያዙም።
******
፬፡ ወጠባባትሰ ነሥኣ ቅብዓ ምስለ መኃትዊሆን በገማዕዊሆን።
******
፬፡ ልባሞች ግን ከፋናቸው ጋራ በማሰሯቸው ዘይት ይዘዋል፡፡
(ሐተታ) ዓብዳት የሚላቸው ሃይማኖት ጾም ጸሎት ትሕትና ኃፊረ ገጽን ይዘው ፮ተኛ በልቡናቸው ፍቅርን ያልያዙ ናቸው። ኃፊረ ገጽና ትሕትናስ አንድ ወገን ናቸው ብሎ ሃይማኖት ጾም ጸሎት ትሕትና ኃፊረ ገጽ አንድ ወገን ንጽሕናን ይዘው ፮ተኛ በልቡናቸው ፍቅርን ያልያዙ ናቸው። ጠባባት የሚላቸው አምስቱን ይዘው ስድስተኛ በልቡናቸው ፍቅርን የያዙ ናቸው። ቅብዕ ኢይርኀቀ ቅብዕሰ ፍቅረ ደቂቀ እጓለ እመሕያው እንዲል። አምስቱን ይዛችሁ ስድስተኛ በልቡናችሁ ፍቅርን ከልያዛችሁ አይሆንም ይሏቸዋል ከነግህ ከሠለስት እንይዛለን ሲሉ ሞት ይመጣባቸዋል። እኒያ አለመጠቀማቸውን እነዚህ መጠቀማቸውን መናገር ነው።
******
፭፡ ወጐንድዮ መርዓዊ ደቀሳ ኵሎን ወኖማ።
******
፭፡ ሙሽራው በዘገየ ጊዜ ዓብዳትም ጠባባትም ተኙ።
******
፮፡ ወከዊኖ መንፈቀ ሌሊት ውውዓ ኮነ ናሁ መርዓዊ መጽአ ፃዑ ተቀበሉ።
******
፮፡ መንፈቀ ሌሊት ሲሆን ሙሽራው መጥቷልና ወጥታችሁ ተቀበሉ ተብሎ ተነገረ።
(ሐተታ) በሀገራቸው ሙሽራ የሚመጣ በመንፈቀ ሌሊት ነውና፡፡
******
፯፡ ወእምዝ ነቅሓ እልኩ ደናግል ኵሎን ወአሠነያ መኃትዊሆን ወወፅኣ ውስተ ቀበላ መርዓዊ።
******
፯፡ ከዚህ በኋላ ልባሞች ተነሥተው ፋናቸውን አዘጋጅተው ሙሽራውን ሊቀበሉ ወጡ።
******
፰፡ ወእልኩ ዓብዳት ይቤላሆን ለጠባባት ሀባነ ቅብዓ አምቅብዕክን።
******
፰፡ ሰነፎች ልባሞችን ከዘይታችሁ ዘይት ስጡን አሏቸው።
እስመ መኀትዊነ ጠፍአነ።
ዘይት አልቆብናልና ።
******
፱፡ ወአውሥኣሆን ጠባባት አንዘ ይብላ አልቦ ዘየአክል ለነ ወለክን
******
፱፡ ልባሞች ለኛና ለእናንተ የሚበቃ ዘይት አልያዝንምና።
አላ ሑራ ወተሣየጣ ለክን እምኀበ እለ ይሠይጡ።
ሄዳችሁ ዘይት ከሚሸጡ ግዙ እንጂ አሏቸው።
******
፲፡ ወሐዊሮን ይሣየጣ በጽሐ መርዓዊ።
******
፲፡ ለጊዜው ሂደው ሳሉ ሙሽራው መጣ።
ወቦአ ምስሌሁ እልኩ እለ ድልዋት ውስተ ከብካብ።
የተዘጋጁ ከሱ ጋራ እንደ እሱ ወደ ሰርግ ገቡ።
ወተአፅወ ኆኅት
ደጅ ተዘጋ።
******
፲፩፡ ወድኅረ መጽኣ እልኩሂ ደናግል ወይቤላ እግዚኦ እግዚኦ አርኅወነ።
******
፲፩፡ እነዚያ ከገቡ ደጅ ከተዘጋ በኋላ ሰነፎች መጥተው ክፈትልን ማለት እንድንገባ አድርገን አሉት።
******
፲፪፡ ወአውሥኦን።
******
፲፪፡ መለሰላቸው
ወይቤሎን አማን እብለክን ከመ ኢየአምረክን።
አላውቃችሁም ብዬ እንዳላውቃችሁ በእውነት እነግራችኋለሁ፡፡
እስመ ስእንክን ተጊሃ ወአምስዮ አሐተ ሰዓተ ምስሌየ።
ተግታችሁ ሥራ አልሠራችሁም ከእኔ ጋራ አንዲት ሰዓት መቆም መቆየት አልተቻላችሁምና፡፡
******
፲፫፡ ትግሁኬ እስመ ኢተአምሩ ዕለታ ወሰዓታ እንተ ባቲ ይመጽእ ወልደ እጓለ አመሕያው፡፡ ማር ፲፫፥፴፫፡፡
******
፲፫፡ ወልደ እጓለእመሕያው ክርስቶስ የሚመጣበትን ዕለት ሰዓት አታውቁምና ለትሩፋት ተግታችሁ ኑሩ።
አንድም ወጐንድዮ መርዓዊ ብለህ መልስ ምጽአት በዘገየ ጊዜ ምእመናን ሁሉ መሞታቸውን መናገር ነው።
ወከዊኖ መንፈቀ ሌሊት
በማዕከለ ዘመን መርዓዊ ክርስቶስ መጥቷልና ለተዋሕዶ የሚያበቃ ሥራ ሥሩ ተብሎ ተነገረ።
(ሐተታ) ያልተካከለ መንፈቅ ነው ወንፍቃ ለሌሊት ወመንፈቆሙ ናፈቁ እንዲል። ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዕለተ ምጽአት ያለውን አንድ ወገን፤ ከምጽአት በኋላ ያለውን አንድ ወገን አድርጎ መንፈቅ አለ።
አንድም የተካከለ መንፈቅ ነው ዓለም ሳይፈጠር ያለውንና ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ያለውን አንድ ወገን ከምጽአት በኋላ ያለውን አንድ ወገን አድርጎ ተናገረ። የዚያ ጥንቱ እንዳይታወቅ የዚህም ፍጻሜው አይታወቅምና። የቊጥር መጽሐፍ ክፍለ ዳግም መንፈቅ ይላል ተአምረ ኢየሱስ ወበ፮ ሰዓተ ሌሊት ተንሥአ እግዚእ ኢየሱስ ይላልሳ ቢሉ ሦስት ሰዓት አሳልፎ ነው መከራ መቀበል የጀመረ። ከዚያ ተነሥቶ ቊጥሮ ፮ አለ እንጂ፡፡ ልደቱም፣ ጥምቀቱም፣ ትንሣኤውም፣ ምጽአቱም በዐሥረኛው ሰዓት ነው።
ወእምዝ ተንሥአ
ለተዋሕዶ የሚያበቃ ሠርተው
ሀባነ ቅብዓ
ከሥራችሁ አትርፉልን፤
እስመ መኃትዊነ ጠፍአነ፡
ለተዋሕዶ የሚያበቃ ሥራ አልሠራንምና ማለት በአንዱ ሥራ አንዱ የሚጠቀም እንደመሰላቸው መናገር ነው
ወአውሥኣሆን እንዘ ይብላ አልቦ ዘየአክል ለነ ወለክን፤
ለእኛና ለእናንተ የሚበቃ ሥራ የለንም አሏቸው ማለት በአንዱ ሥራ አንዱ እንዳይጠቀም ማወቃቸውን መናገር ነው፤
አላ ሑራ
ምሕረትን ከሚያድሉ ከሥላሴ ምሕረትን ከሚያሰጡ ከነዳያን ለምኑ እንጂ አሏቸው፤
ወሐዊርሮን ይሣየጣ፤
ነግህ ሠልስት ሥራ እንሠራለን ሲሉ ምጽአት ደረሰ።
ወቦአ ምሰሌሁ፤
ሥራ ሠርተው የተገኙት ተዋሐዱት ተዋሐዳቸው።
ወተአጽወ ኆኅት
ምሕረት ተከለከለ፤
ወድኅረ መጽኣ ወይቤላ አርኅወነ፤
የሚገቡ እንደመሰላቸው መናገር ነው፤
ወአውሥኦን
አላውቃችሁም ብዬ እንዳላውቃችሁ በእውነት አነግራችኋለሁ፤ ፈጥሮስ አላውቃችሁም ማለት አይመችም ብሎ ወለድኳችሁ ካድኳችሁ እላቸዋለሁ።
እስመ ስእንክን ተጊሃ
ለተዋሕዶ የሚያበቃ ሥራ አልሠራችሁምና ትግሁኬ እንዳለፈው።
(ሐተታ) አብዳት የሚላቸው ሃይማኖት እንበለ ምግባር ንጽሐ ሥጋ እንበለ ንጽሐ ነፍስ ፍቅር እንበለ ተስፋ ምሕረት እንበለ ትዕግሥት ጸሎት ዘምስለ ትምክህት የያዙ ናቸው። ጠባባት የሚላቸው ሃይማኖት ዘምስለ ምግባር ንጽሐ ሥጋ ዘምስለ ንጽሐ ነፍስ። ምሕረት ዘምስለ ትዕግሥት ፍቅር ዘምስለ ተስፋ ጸሎት እንበለ ትምክህት የያዙ ናቸው፡፡ ይህን ይዛችሁ ይህን ካልያዛችሁ አይሆንም ይሏቸዋል። ከነግህ ከሠለስት እንይዛለን ሲሉ ሞት ይመጣባቸዋል እኒህ መጠቀማቸውን እኒያ አለመጠቀማቸውን መናገር ነው።
አንድም አብዳት የሚላቸው አእምሮ ለብዎ ሰሚዕ ምሕረት ትዕግሥት እኒህን አምስቱን ይዘው አሚን ተስፋ ፍሥሐ ሰላም ፍቅርን ያልያዙ ናቸው፡፡ ጠባባት የሚላቸው ዓሥሩንም የያዙ ናቸው፡፡ ይኸን ይዛችሁ ይኸን ካልያዛችሁ አይሆንም ይሏቸዋል። ከነግህ ከሠለስት እንይዛለን ሲሉ ሞት ይመጣባቸዋል እኒህ መጠቀማቸውን እኒያ አለመጠቀማቸውን መናገር ነው፡፡
አንድም አብዳት የሚላቸው አይሁድ ተንባላት ናቸው፤ ጠባባት የሚላቸው ክርስቲያን ናቸው ካላመናችሁ ከልተጠመቃችሁ አይሆንም ይሏቸዋል ከነግህ ከሠለስት እንጠመቃለን ሲሉ ሞት ይመጣባቸዋል እኒህ መጠቀማቸውን እኒያ አለመጠቀማቸውን መናገር ነው።
አንድም አብዳት የሚላቸው አምነው ተጠምቀው የክርስቲያን ሥራ የማይሠሩ ናቸው፡፡ ጠባባት የሚላቸው አምነው ተጠምቀው ሥራ የሚሠሩ ናቸው፡፡ አምናችሁ ተጠምቃችሁ ሥራ ከአልሠራችሁ አይሆንም ይሏቸዋል፡፡ ከነግህ ከሠለስት እንሠራለን ሲሉ ሞት ይመጣባቸዋል እኒህ መጠቀማቸውን እኒያ አለመጠቀማቸውን መናገር ነው።
******
በእንተ ምሳሌ ዘመካልይ።
፲፬፡ እስመ ከመ ብእሲ ዘይነግድ ወጸውአ አግብርቲሁ ወወሀቦሙ ንዋዮ ይትገበሩ ቦቱ። ሉቃ ፲፱፥፲፪፡፡
፲፬፡ መንግሥተ ሰማይ ሕገ ወንጌል፣ ሕገ ወንጌል ተስፋ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ብላቴኖችን ጠርቶ ወጥተው ወርደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን የሰጣቸውን ነጋዴን ትመስላለችና ትግሁ። አንድም ትመስላለችኮን።
******
ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
14/10/2011 ዓ.ም