Monday, April 22, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 73
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 72
Sunday, April 21, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 71
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
******
፩፡ ወጸውዖሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ አርዳኢሁ፡፡ ማር ፫፥፲፫፡፡ ሉቃ ፮፥፲፫፡፡ ፱፥፩፡፡
******
፩፡ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ጸራቸው፡፡ ማለት ሾማቸው፡፡
ወወሀቦሙ ሥልጣነ ዲበ መናፍስት ርኩሳን ከመ ያውፅእዎሙ ወይፈውሱ ኵሎ ድውያነ ወሕሙማነ።
አጋንንት ያወጡ ድውያን ይፈውሱ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው ማለት ለሹመታቸው ምልክት ዱያነ ፈውሱ ሙታነ አንሥኡ እለ ለምጽ አንጽሑ ብሎ ገቢረ ታምራትን ሰጣቸው፤ ንጉሥ ደጃዝማች በሾመ ጊዜ ለሹመቱ ምልክት ሰንደቅ አላማ ማሠሬ ነጋሪት ሰጥቶ እንዲሰደው። አሥራ ሁለት መሆናቸው ስለምን ቢሉ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም።
ትንቢት፤ ኤርምያስ ለሊሁ ኢየሱስ ይመጽእ ውስተ ዓለም ወየኀሪ ፲ወ፪ተ ሐዋርያተ ወይከይድ ውስተ ደብረ ዘይት ዘአነ ርኢኩ ሥግወ ብሏል። ኤልሳዕም በራእዩ ወናሁ ይወርድ እግዚእነ እምሰማይ ዲበ ምድር ወየኅሪ ፲ተ ወ፪ተ ዕፀወ ባሉጥ ብሏል።
ምሳሌም ያዕቆብ ከአዋልደ ከነዓን አልተጋባም ሶርያ ወርዶ ፲፪ት ሕፃናት ወልዷል ጌታም ባሕርየ መላእክትን ባሕርይ አላደረገም የአዳምን ባሕርይ ባሕርይ አድርጎ አሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ሹሞ መስደዱን መናገር ነው። ኢነሥኦ ለዘነሥኦ እመላእክት ዘእንበለ ዳዕሙ እምዘርአ አብርሃም እንዲል። ለነዚያ ሦስት ምውታን አሥራው አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ አሏቸው ለኒህም ሦስት ሕያዋን አሥራው ሥላሴ አሏቸውና በአሥራ ሁለቱ ምዕዛረ ፀሐይ በአሥራ ሁለቱ አልህምተ ብርት በአሥራ ሁለቱ መገብተ ሰሎሞን በአሥራ ሁለቱ የቤት አለቆች በአሥራ ሁለቱ ጉበኞች ምሳሌ። ወግዕዙ እስራኤል ወበጽሑ ኀበ ቦ ፲ ወ፪ቱ አንቅዕት ወ፸ ተመርት ይላል። አሥራ ሁለቱ አንቅዕት ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ፸ ተመርት የ፸ አርድዕት ምሳሌ።
አንድም በልብሰ አሮን ባሉ በአሥራ ሁለቱ አዕናቊ ምሳሌ። በደብረ ሲና ከዙፋኑ እግር በተገኙ በ፲፪ቱ አዕናቊ፤ ኤልያስም ፬ ቻል ውሃ አምጡ ብሎ ድግሙ ሠልሱ ብሏቸዋል በዚያ ምሳሌ ኢያሱ ዮርዳኖስን ሲሻገር አሥራ ሁለት ድንጊያ ከአፍአ አግብቶ በውስጥ ተክሏል አሥራ ሁለት ድንጊያ ከባሕሩ አውጥቶ አሸክሞ ወስዶ ፮ን በጌባል ፮ን በገሪዛን አሰተክሏቸዋል ሰዎቹ የሐዋርያት ድንጊያው የመከራቸው ምሳሌ። ትንቢቱን አውቆ አናግሯል ምሳሌውንም እንጂ ባወቀ አስመስሏል ምሥጢሩ እንደምን ነው ቢሉ ለ፬ ባሕርያት ሦስት ሦስት ግብር አላቸው። አሥራ ሁለት ይሆናል ካራቱ ባሕርያት የተፈጠረ ሰውን እጠብቅባቸዋለሁ ሲል።
******
፪፡ ወዝውእቱ አስማቲሆሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ ሐዋርያት።
******
፪፡ ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ስማቸው ይሀ ነው። ሐዋርያት ማለት ደጃዝማች ቀላጤ ምጥው ፍንው ሃያጂ ማለት ነው። ደጃዝማች በተሾመበት አገር ገብቶ የተቀበለውን ሹመት ሽልማት ሰጥቶ ያከብረዋል። ካሀን ቢሆን አስራቱን በኩራቱን ሰጥቶ ያከብረዋል። ይህን የማይሻ መነኩሴ ቢሆን ከእግሩ ወድቆ አቡነ ዘበሰማያት ይቀበላል ለመነኩሴው ክብሩ ነው ያልተቀበለውን ዓይን በፍላት እጅ እግር በስለት ይቀጣል።
ሐዋርያት ትምርታቸውን የተቀበሏቸውን በልጅነት ያከብራሉ ሀብት ሥርየት ይሰጣሉ ያልተቀበሏቸውን በሌጌዎን ይነጻሉ በነፋስ ይሰቅላሉና። ቀላጤም፤ በደለኛ ወታደር ካልገዛው አገር ገብቶ ያልፈላ ያስጠምቃል ያልቦካ ያስጋግራል፤ የተበደለ ድሃ ከንጉሥ ሄዶ ይጮሃል ባዳራሽ ተገኝቶ ቀላጤ ሰጥቶ ይሰደዋል ያ ቀላጤ ባብርሃን የገባውን በጨለማ በፀሐይ የገባውን በዝናም አስወጥቶ የተሰበረ እንጨቱን የተቀዳ ውሀውን ያስመልስለታል። በደለኛ ወታደር ካልገዛው አገር ገብቶ ያልፈላ እንዲያስጠምቅ ያልቦካ እንዲያስጋግር ዲያብሎስ ያልፈጠፈውን ፍጥረት ያልገዛውን ሰውነት ፭ ሽህ ከ፭፻ ዘመን ኃጢአት ሲያሰራ ጣዖት ሲያስመልክ መኖሩን መናገር ነው፡፡ የተበደለ ድሃ ከንጉሥ ሂዶ እንደመጮህ ነቢያት አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ ማለታቸውን መናገር ነው ንጉሥ ባዳራሽ ተገኝቶ ቀላጤ ሰጥቶ እንደመስደድ ቃለ እግዚአብሔር ሰው ሁኖ አሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ሹሞ መስደዱን መናገር ነው። ቀላጤ በብርሃን የገባውን በጨለማ በፀሐይ የገባውን በዝናም እንዲያስወጣ ሐዋርያትም በደዌ የገባውን በታምራት በክህደት የገባውን በትምርት ማስወጣታቸውን መናገር ነው። የተሰበረ እንጨቱን እንዲያስመልስለት በአዳም የሄደውን ልጅነት አስመልሰዋልና ፍንው፤ ወናሁ አነ እፌንወክሙ ከመ አባግዕ ማዕከለ ተኵላት ብሎ እንዲያመጣው ምጥው ከፍንው ይገባል ሃያጅም አለ ይህ ሁሉ ካልሄዱ አይገኝምና።
ቀዳሚ ስምዖን ዘተሰምየ ጴጥሮስ።
አንዱ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለ ስምዖን ነው። (ሐተታ) ጴጥሮስ ማለት መርግ ማለት ነው መርግ ከወደላይ ሲመጣ ያስፈራል። እሱም ሞተ በሥጋ ወሐይወ በመንፈስ እያለ ሲያስተምር ያስፈራልና።
አንድም ሻፎ ደንጊያ ማለት ነው ይህ ሥጋን ከአጥንት ይለያል። እሱም ምዕመናንን ከመናፍቃን ይለያልና።
አንድም ደንጊያ ማለት ነው ይህን የቀን ሐሩር የሌሊት ቊር አይለውጠውም። እሱም በመከራ አይለወጥምና።
አንድም ከዋው ደንጊያ ማለት ነው ያ እየፈጋ ይሄዳል። እሱም ከ፲፩ዱ ስብከት ሁሉ እየገባ ያስተምራልና።
ወእንድርያስ እኊሁ።
ወንድሙ እንድርያስ ነው። (ሐተታ) እንድርያስ ማለት ተባዕ ለመስቀል በኵረ ሐዋርያት ማለት ነው።
******
፫፡ ወያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
፫፡ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ነው
******
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
13/08/2011 ዓ.ም
Saturday, April 20, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 70
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ መጻጒዕ።
ምዕራፍ ፱።
******
በእንተ ጽሙም ዘቦቱ ጋኔን
፴፪፡ ወእምዝ አምጽኡ ኀቤሁ ዘጋኔን ፅሙመ ወበሀመ። ማቴዎ ፲፪፥፳፪፡፡ ሉቃ ፲፩፥፲፬።
******
፴፪፡ ከዚህ በኋላ ጋኔን ድዳ ደንቆሮ ያደረገውን ሰው ይዘው መጡ። ድዳ ደንቆሮ ጋኔን ሲያድርበት ሰውም ድዳ ደንቆሮ ይሆናልና።
አንድም ጽሙም ወበሐም ይላል ድዳ ደንቆሮ ጋኔን ያደረበትን ሰው ይዘው መጡ። ቀድስ ቢሉት አልቀድስም ብሏልና ድዳ አለው። ትእዛዘ እግዚአብሔርን ስማ ቢሉት አልሰማም ብሏልና ደንቆሮ አለው።
******
፴፫፡ ወወፂኦ ጋኔኑ ነበበ ውእቱ በሐም ወሰምን ውእቱ ጽሙም
******
፴፫፡ ጋኔኑ በተለየው ጊዜ ድዳ የነበረው ተናገረ ደንቆሮ የነበረው ሰማ።
******
፴፬፡ ወፈሪሳውያንሰ ይቤሉ በመልአኮሙ ለአጋንንት ያወፅኦሙ ለአጋንንት።
******
፴፬፡ ፈሪሳውያን ግን ታምራት ያደርጋል ሰው ይሳባል ኦሪት ትጠፋለች ወንጌል ትሰፋለች ብለው የንጉሥን ጭፍራ በንጉሥ ቀላጤ እንዲያስወጡት ከአለቃቸው ከብዔል ዜቡል ተጨዋውቶ ያስወጣቸዋል እንጂ አለዚያ ግን አያስወጣቸውም አሉ። አሁን ለነዚህ ዛሬ አይመልስላቸውም በሚመጣው ጉባዔ ይመልስላቸዋል
******
በከመ አንሶሰወ ኢየሱስ ውስተ ገሊላ።
፴፭፡ ወአንሶሰወ እግዚእ ኢየሱስ ውስተ ኵሉ አህጉር ወበሐውርት እንዘ ይሜህር በምኵራባቲሆሙ። ማር ፮፥፮።
******
፴፭፡ በምኵራባቸው እየገባ ሲያስተምር ኖረ
ወይሰብክ ወንጌለ መንግሥት
ጌትነቱን የምትናገር ወንጌልን ሲያስተምር ኖረ። (ሐተታ) እንዳለፈው። ምዕ ፬ ቊ ፳፫፡፡
ወይፈውስ ኵሎ ድውያነ ወኵሎ ሕማመ ዘውስተ ሕዝብ ለዚያው ምልክት በሕዝቡ ዘንድ ያሉ ድውያንን ሁሉ ይፈውስ ነበረ።
******
፴፮፡ ወርእዮ ብዙኃነ ሰብአ አምህርዎ ወተሣሃሎሙ።
******
፴፮፡ ብዙ ሰዎችን ባየ ጊዜ አሳዘኑት አዘነላቸው።
እስመ ስሩሃን እሙንቱ።
በፃማ ኦሪት በፃማ ኃጢአት ደክመዋልና።
ወግዱፋን ከመ አባግዕ ዘአልቦ ኖላዊ፡፡
ጠባቂ እንደሌላቸው አባግዕ ሁነዋልና።
******
፴፯፡ ወእምዝ ይቤሎሙ ለአርዳኢሁ። ሉቃስ ፪፥፪።
******
፴፯፡ ከዚህ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ አንዲህ አላቸው፤
ማዕረሩሰ ብዙኅ
መከሩ ብዙ ነው
ወገባሩ ኅዳጥ።
ሠራተኛው ግን ጥቂት ነው።
******
፴፰፡ ሰአልዎ ለበዓለ ማዕረር።
******
፴፰፡ የመከሩን ባለቤት ለምኑት።
ከመ ይወስክ ገባረ ለማዕረሩ።
ለመከሩ አጫጅ ሠራተኛ ይጨምር ዘንድ።
አንድም ማዕረሩሰ ብዙኀ ሰማዕያኑ ብዙ ናቸሙ። ወገባሩ ኅዳጥ መምሩ አንድ ዮሐንስ ነው ወኅዳጥ ዓሣ እንዲል። ሰአልዎ የመምህርነት ባለቤት እኔን ለምኑኝ።
ከመ ይዌስክ እናንቱን መምራን አድርጌ አስነሣችሁ ዘንድ ወደፊት በሚያመጣው ሹመት አትለምኑ ይል የለም ከዚህ ምነው እንዲህ አለ ቢሉ። ያ ሥጋዊ ነው ይህ ግን መንፈሳዊ ነውና የሚጠቀሙበትም ነውና።
አንድም አስፈቅዶ ለመሾም መከራ በመጣባቸው ጊዜ ተሾሙ ተሾሙ ያለን ለዚህ ነው እንዳይሉ። ምነዋ መከራ ብንቀበል ወደን እንጂ ተሹመነዋል እንዲሉ።
አንድም ማዕረሩ ብዙኅ መጻሕፍተ ነቢያት ንባባቸው ብዙ ነው። ወገባሩ ሕዳጥ ትርጓሜያቸው ጥቂት ነው። ድኅነት አያሰጡም። ሰአልዎ የብሉይ የሐዲስ ባለቤት እኔን ለምኑኝ። ከመ ይወስክ ገባረ። መተርጉማን አድርጌ አስነሣችሁ ዘንድ ድነት እንድታሰጡ አደርጋችሁ ዘንድ፡፡
******
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
፩፡ ወጸውዖሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ አርዳኢሁ፡፡ ማር ፫፥፲፫፡፡ ሉቃ ፮፥፲፫፡፡ ፱፥፩፡፡
፩፡ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ጸራቸው፡፡ ማለት ሾማቸው፡፡
******
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
12/08/2011 ዓ.ም