Monday, April 22, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 73

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
                   ******    
፯፡ ወሐዊረክሙ ስብኩ እንዘ ትብሉ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት
                   ******    
፯፡ ሂዳችሁ ደጊቱ በልጅነት ልጅነት በሃይማኖት የምትሰጥበት ጊዜ ደርሷል እያላችሁ አስተምሩ።
                   ******
  ፰፡ ድውያነ ፈውሱ።
                   ******    
፰፡ ድውያንን ፈውሱ።
ሙታነ አንሥኡ።
ሙት አንሡ።
እለ ለምጽ አንጽሑ።
ለምጽ አድኑ
አጋንንተ አውጽኡ።
አጋንንትን አውጡ፥
በጸጋ ዘነሣእአክሙ በጸጋ ሀቡ
በለጋስነት የተማራችሁትን በለጋስነት አስተምሩ።
በከንቱ ዘነሣዕክሙ በከንቱ ሀቡ
ዋጋ ሳትሰጡ የተማራችሁትን ዋጋ ሳትቀበሉ አስተምሩ፡፡
አንድም በጸጋ ዘነሣእክሙ በታምራት የተማራችሁትን በታምራት አስተምሩ በከንቱ ዘነሣእክሙ ሳትጥሩ የተማራችሁትን ሳይጥሩ አስተምሩ
                   ******    
፱፡ ኢታጥርዩ ለክሙ ወርቀ ወኢብሩረ ማር ፮፥፰፡፡ ሉቃ ፱፥፫፡፡ ፲፥፬፡፡
                   ******    
፱፡ ወርቅ ብር አትያዙ
ወኢጸሪቀ ውስተ ቅናውቲክሙ፡፡
 በዝናራችሁ ቊናማቲክሙ ይላል። በተረንተራችሁ ሻሜ መሐልቅ አትያዙ።
                   ******    
፲፡ ወኢጽፍነተ ለፍኖት።
                   ******    
፲፡ የስንቅ አቅማዳም አትያዙ።
ወኢ፪ኤ ክዳናተ።
ሁለት ልብስም አትያዙ። ይህን የሚሹ ሥጋውያን ናቸው እሳቸው ግን መንፈሳውያን ናቸውና ይህን አይሹም።
አንድም ሁለት ልብስ ባይኖረን አንዱን ለብሰን አንዱን ሽጠን ባንመገብ እንደምን በሆነ ነበር ብሎ ያዳክማልና እንዳያዳክማቸው ነው፡፡
ወኢዓሣዕነ።
ጫማ አታድርጉ ይህ ለሥጋውያን ነው እሳቸው ግን መንፈሳውያን ናቸውና ደህን አይሹትም።
አንድም ጫማ ባይኖረን እሾሁን እንቅፋቱን ዋዕዩን እንደምን ባለፍነው ነበር ብሎ ያዳክማልና አንዳያዳክማቸው ነው።
አንድም ጌጸኛውን ሲል ነው።
ወኢበትረ።
በትርም አትያዙ። ይህ ለሥጋውያን ነው እሳቸው ግን መንፈሳውያን ናቸውና ይህን አይሹትም።
አንድም በትር ባንይዝ ውሻው እባቡ እንደምን ባደረገን ነበር ብሎ ሃይማኖት ያዳክማልና እንዳያዳክም ነው
አንድም ጌጸኛውን ሲል ነው
እስመ ይደልዎ አስቡ ለዘይትቀነይ።
ለሚሠራ ዋጋ ይገባዋልና ለሚያስተምር መምህር የለት ራት አንድ እንጀራ ጽዋ ውሀ ይገባዋልና።
ኢታጥርዩ።
አንድም ስናስተምር ውለን ምን እንመገባለን ትሉኝ እንደሆነ ለሚያስተምር ለመምህር እንጂ የዕለት ራት አንድ እንጀራ ጽዋ ውሀ ይገባዋል እነዚያው ይመግቧችሁ።
                   ******    
፲፩፡ ወውስተ ሀገር እንተ ቦእክሙ ወእመኒ አብያት ተስአሉ ወበሉ ለመኑ ይደልዎ ሰላም በውስቴታ።
                   ******    
፲፩፡ ከገባችሁበት አገር ከገባችሁበት ቤት ደግ ሰው የበቃ ማን አለ ብላችሁ ጠይቁ።
ወህየ ኅድሩ እስከ አመ ትወጽኡ።
ለማስተማር ወጥታችሁ እስክትሄዱ ድረስ ከዚያ ኑሩ።
(ሐተታ) ምዕመናን ለመማር በመጡ ጊዜ እንዳያጧቸው ነው።
አንድም ከአንዱ ወደ አንዱ ሲሉ ያይዋቸው እንደሆነ እኒህማ ምግብ ለማሻሻል መጥተዋል እንጂ መቼ ለማስተማር መጥተዋል እንዳይሏቸው።
                   ******    
፲፪፡ ወበዊአክሙ ውስተ ቤት ተአምኅዎሙ።
                   ******    
፲፪፡ ከቤት በገባችሁም ጊዜ እጅ ንሷቸው ማለት አክብሯቸው እንጂ አክብሩን አትበሉ።
ወለእመ ይደልዎ ለውእቱ ቤት ይኅድር ሰላምክሙ ላዕሌሁ
የበቃ ደግ ሰው የተገኘ እንደሆነ ሰላማችሁ እኔ አድርበታለሁ
                   ******    
፲፫፡ ወእመሰ ኢይደልዎ ይግባእ ሰላምክሙ ላዕሌክሙ
                   ******    
፲፫፡  የበቃ ደግ ሰው ያልተገኘ እንደሆነ ግን ሰላማችሁ በናንተ ይደር ማለት ሰላማችሁ እኔ በናንተ እንዳደደርኩ እቀራለሁ።
                   ******    
፲፬፡ ወለዘሰ ኢተወክፈክሙ ወኢሰምዓ ነገረክሙ ወፂአክሙ አፍአ እምውእቱ ቤት ወእም ውእቱ ሀገር ንግፉ ፀበለ እገሪክሙ።
                   ******    
፲፬፡ እናንተን አልቀበልም ትምህርታችሁንም አልሰማም ያለ ሰው ካለበት ቤት ካለበት አገር ወጥታችሁ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ።
(ሐተታ) ስንኳን ገንዘባችሁ ትቢያችሁ አልተከተለንም ለማለት። እኛ ደክመንላችሁ በእምቢታችሁ ቢቀርባችሁ ፍዳችሁ በራሳችሁ ነው ለማለት።
አንድም ይህ ትቢያ ከኛ እንደተለየ እናንተም ከኛ ልዩ ናችሁ ለማለት፡፡
አንድም ትቢያ እንደ ረገፈ እናንተም በሥጋችሁ በመቅሰፍት በነፍሳችሁ በገሃነም ትጠፋላችሁ ለማለት፡፡
አንድም በቄሣር ልማድ የተበደለ ሰው ቢኖር እንጨት ተክሎ ሣር ቋጥሮ መጥቶ ይንገረኝ ብሎ ነበርና።
                   ******    
፲፭፡ አማን እብለክሙ ከመ ይረክባ ሳሕተ ምድረ ሰዶም ወገሞራ አመ ዕለተ ደይን ፈድፋደ እምይእቲ ሀገር።
                   ******    
፲፭፡ እናንተን አልቀበልም ትምህርታችሁን አልሰማም ያለ ሰው ሁሉ ካለበት አገር ይልቅ ሰዶም ገሞራ በፍርድ ቀን ዕረፍትን ያገኛሉ ብዬ እንዲያገኙ በእውነት እነግራችኋለሁ። በሀገሩ ሰዎቹን መናገር ነው ፍዳ ይቀልላቸዋል ማለት ነው።
                   ******    
፲፮፡ ወናሁ አነ እፌንወክሙ ከመ አባግዕ ማዕከለ ተኲላት። ሉቃ ፲፥፫፡፡
፲፮፡ ተኲላ አለና ብለው አባግዕን ከቤት እንዳያውሏቸው ተኲላ ወዳለበት እንዲያሰማሯቸው፡፡
                   ******      
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
15/08/2011 ዓ.ም

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 72

==================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
                   ******    
፫፡ ወያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
                   ******    
፫፡ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ነው (ሐተታ) ያዕቆብ ማለት አዕቃጺ አኃዚ ማለት ነው። የቀደመው ያዕቆብ ሰኰና ኤሳውን ይዞ እንደተወለደ። እሱም ሰኰና ወንጌልን ይዞ ሲያስተምር ይሞታልና። ሰኰና ኤሳውን እንዳሰናከለ እሱም የመናፍቃንን ትምህርት ያሰናክላልና፡፡
ወዮሐንስ እኊሁ።
ወንድሙ ዮሐንስ ነው። ዮሐንስ ማለት ፍሥሐ ወኀሤት ማለት ነው። ወብዙኃን ይትፌሥሑ በልደቱ እንዲል።
ፊልስጶስ
ፊልጶስ ነው ፊልጶስ ማለት ረያጼ አፍራስ ማለት ነው አኃዜ ኵናትም ማለት ነው መፍቀሬ አኃው ማለት ነው ፊልሳዳፎስ እንዲል።
ወበርተሎሜዎስ።
በርተሎሜዎስ ነው በእብራይስጥ በር ልጅ ማለት ነው። ተክል የማጠጣት ግብር ያለው ልጅ ማለት ነው ወልደ ኃይል ወልደ የማን እንዲል። አንድም ወይን ተክሎ ዕለቱን አድርሷልና።
ቶማስ
ቶማስ ነው ቶማስ ማለት ፀሐይ ማለት ነው። ፪ቱ አስማቲሁ ለፀሐይ አሐዱ ቶማስሰ ወ፩ዱ ኦርያሬስ አንዲል።
ወማቴዎስ መጸብሐዊ
አንዱ ማቴዎስ ነው። ማቴዎስ ማለት ኅሩይ ማለት ነው ከዚህ አውጥቶ ለዚህ መዓርግ አበቃው ለማለት ስሙን ከነግብሩ ጠራው፡፡
ወያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ።
የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ ነው (ሐተታ) እንዳለፈው።
ወልብድዮስ ዘተሰምየ ታዴዎስ፡፡
ታዴዎስ የተባለ ልብድዮስ ነው ልብድዮስ ማለት ልብደ ሠሪ ዓሣ ወጋሪ ማለት ነው። ልበ ድዮስ ይላል ካህነ አምላክ ማለት ነው። ወአምጽኡ ማሬ ዘድዮስ ለ፲ወ፪ቱ ሕዝበ ድዮስጶራ እንዲል።
አንድም ዘርዕ ወማዕረር ማለት ነው ኦሪትን እንደ ዘር ወንጌልን እንደ መከር አድርጎ አስተምሯልና፡፡
አንድም ስንዴ ዘርቶ ዕለቱን ለመሥዋዕት አድርሷልና፡፡
                   ******    
፬፡ ወስምዖን ቀነናዊ።
                   ******    
፬፡ ባልተነበበ ስሙ ይተረጉማሉ ስምዖን ያለው ናትናኤል ነው፡፡ ናትናኤል ማለት ውሁብ ሀብተ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ቀነናዊ የቃና ሰው ቀሬናዊ የቀራንዮ ሰው ቀናዒ ለሕገ አምላኩ።
ወይሁዳ አስቆሮታዊ ዘውእቱ አግብኦ።
የአስቆሮት ሰው የሚሆን ያስያዘው ይሁዳ ነው። ይህ ሰው ስሙ ከግብሩ ያልተባበረ ነው፡፡ ይሁዳ ማለት ተአማኒ በእግዚአብሔር ማለት ነበር እሱ ግን አላደረገውም ለዚህ መዓርግ ቢያበቃው ከሞቱ ገባበት ለማለት ጻፈው እንዳወጣው ለማጠየቅ በመጨረሻ አመጣው።
                   ******    
፭፡ እሎንተ አሠርተ ወ፪ተ ሐዋርያተ ፈነዎሙ እግዚእ ኢየሱስ።
                   ******    
፭፡ እሎንተ ካለ ፈነወ ፈነዎሙ ካለ ለእሎንቱ ባለ በቀና ነበር። ጌታ እኒህን ፲፪ቱን ሐዋርያት ላከ ማለት መርጦ ሾመ፡፡
(ሐተታ) ከ፭ ወገን መርጧቸዋል። ከአናምያን ከሓናጽያን ከመጸብሓን ከመሠግራን ከመስተገብራን ቤትን በአምስት ወገን ያጸኑታል በጭቃ በገለባ በሣር በደንጊያ በእንጨት። ከአራት ባሕርያት ከአምስተኛ ባሕርየ ነፍስ የተፈጠረ ሰውን አጸናባችኋለሁ እጠብቅባችኋለሁ ሲል። ከነዚህም ስማቸውን የለወጠውም ያለወጠውም አለ። በኦሪቱ ያሳለፈውም ያላሳለፈውም ግብር እንዳለ ለማጠየቅ። ስም ማውጣትም የገዥና የተገዥ ምልክት ነው ባለቤት ለቤተ ሰው ስሙን ለውጦ እንዲያወጣ
ወአዘዞሙ እንዘ ይብል ፍኖተ አሕዛብ ኢትሑሩ
በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ ማለት የአሕዛብን ሥራ አትሥሩ።
ወውስተ ሀገረ ሳምር ኢትባኡ።
ወደ ሳምራውያንም አገር አት ግቡ ብሎ አዘዛቸው።
                   ******    
፮፡ ወሑሩ ባሕቱ ኀበ አባግዕ ዘተኃጐላ እምቤተ እስራኤል።
                   ******    
፮፡ ከእስራኤል ወደጠፉ በጎች ሂዱ ማለት መምህር አብነት ትምህርት አጥተው ወደ ተጐዱ ወደ እስራኤል ሂዳችሁ አስተምሩ እንጂ ትንቢት የተነገረ ሱባዔ የተቈጠረ ለነዚህ ነውና፡፡
አንድም ትንቢት የተነገረልን ሱባዔ የተቈጠረልን እኛ ሳለን ትምህርቱን ለሌላ ቢያደርገው ከሞቱ ገባንበት ባሉ ነበርና።
አንድም በፍቅር ለመሳብ።
አንድም በመንፈስ ቅዱስ ባልታደሰ ሰውነታቸው መከራ ቢያጸኑባቸው በካዱ ነበርና እንዳይክዱ።
                   ******    
፯፡ ወሐዊረክሙ ስብኩ እንዘ ትብሉ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት
፯፡ ሂዳችሁ ደጊቱ በልጅነት ልጅነት በሃይማኖት የምትሰጥበት ጊዜ ደርሷል እያላችሁ አስተምሩ።
                   ******    
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
14/08/2011 ዓ.ም

Sunday, April 21, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 71

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
                   ******   
፩፡ ወጸውዖሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ አርዳኢሁ፡፡ ማር ፫፥፲፫፡፡ ሉቃ ፮፥፲፫፡፡ ፱፥፩፡፡
                   ******   
፩፡  አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ጸራቸው፡፡ ማለት ሾማቸው፡፡
ወወሀቦሙ ሥልጣነ ዲበ መናፍስት ርኩሳን ከመ ያውፅእዎሙ ወይፈውሱ ኵሎ ድውያነ ወሕሙማነ።
አጋንንት ያወጡ ድውያን ይፈውሱ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው ማለት ለሹመታቸው ምልክት ዱያነ ፈውሱ ሙታነ አንሥኡ እለ ለምጽ አንጽሑ ብሎ ገቢረ ታምራትን ሰጣቸው፤ ንጉሥ ደጃዝማች በሾመ ጊዜ ለሹመቱ ምልክት ሰንደቅ አላማ ማሠሬ ነጋሪት ሰጥቶ እንዲሰደው። አሥራ ሁለት መሆናቸው ስለምን ቢሉ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም።
ትንቢት፤ ኤርምያስ ለሊሁ ኢየሱስ ይመጽእ ውስተ ዓለም ወየኀሪ ፲ወ፪ተ ሐዋርያተ ወይከይድ ውስተ ደብረ ዘይት ዘአነ ርኢኩ ሥግወ ብሏል። ኤልሳዕም በራእዩ ወናሁ ይወርድ እግዚእነ እምሰማይ ዲበ ምድር ወየኅሪ ፲ተ ወ፪ተ ዕፀወ ባሉጥ ብሏል።
ምሳሌም ያዕቆብ ከአዋልደ ከነዓን አልተጋባም ሶርያ ወርዶ ፲፪ት ሕፃናት ወልዷል ጌታም ባሕርየ መላእክትን ባሕርይ አላደረገም የአዳምን ባሕርይ ባሕርይ አድርጎ አሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ሹሞ መስደዱን መናገር ነው። ኢነሥኦ ለዘነሥኦ እመላእክት ዘእንበለ ዳዕሙ እምዘርአ አብርሃም እንዲል። ለነዚያ ሦስት ምውታን አሥራው አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ አሏቸው ለኒህም ሦስት ሕያዋን አሥራው ሥላሴ አሏቸውና በአሥራ ሁለቱ ምዕዛረ ፀሐይ በአሥራ ሁለቱ አልህምተ ብርት በአሥራ ሁለቱ መገብተ ሰሎሞን በአሥራ ሁለቱ የቤት አለቆች በአሥራ ሁለቱ ጉበኞች ምሳሌ። ወግዕዙ እስራኤል ወበጽሑ ኀበ ቦ ፲ ወ፪ቱ አንቅዕት ወ፸ ተመርት ይላል። አሥራ ሁለቱ አንቅዕት ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ፸ ተመርት የ፸ አርድዕት ምሳሌ።
አንድም በልብሰ አሮን ባሉ በአሥራ ሁለቱ አዕናቊ ምሳሌ። በደብረ ሲና ከዙፋኑ እግር በተገኙ በ፲፪ቱ አዕናቊ፤ ኤልያስም ፬ ቻል ውሃ አምጡ ብሎ ድግሙ ሠልሱ ብሏቸዋል በዚያ ምሳሌ ኢያሱ ዮርዳኖስን ሲሻገር አሥራ ሁለት ድንጊያ ከአፍአ አግብቶ በውስጥ ተክሏል አሥራ ሁለት ድንጊያ ከባሕሩ አውጥቶ አሸክሞ ወስዶ ፮ን በጌባል ፮ን በገሪዛን አሰተክሏቸዋል ሰዎቹ የሐዋርያት ድንጊያው የመከራቸው ምሳሌ። ትንቢቱን አውቆ አናግሯል ምሳሌውንም እንጂ ባወቀ አስመስሏል ምሥጢሩ እንደምን ነው ቢሉ ለ፬ ባሕርያት ሦስት ሦስት ግብር አላቸው። አሥራ ሁለት ይሆናል ካራቱ ባሕርያት የተፈጠረ ሰውን እጠብቅባቸዋለሁ ሲል።
                   ******   
፪፡ ወዝውእቱ አስማቲሆሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ ሐዋርያት።
                   ******   
፪፡ ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ስማቸው ይሀ ነው። ሐዋርያት ማለት ደጃዝማች ቀላጤ ምጥው ፍንው ሃያጂ ማለት ነው። ደጃዝማች በተሾመበት አገር ገብቶ የተቀበለውን ሹመት ሽልማት ሰጥቶ ያከብረዋል። ካሀን ቢሆን አስራቱን በኩራቱን ሰጥቶ ያከብረዋል። ይህን የማይሻ መነኩሴ ቢሆን ከእግሩ ወድቆ አቡነ ዘበሰማያት ይቀበላል ለመነኩሴው ክብሩ ነው ያልተቀበለውን ዓይን በፍላት እጅ እግር በስለት ይቀጣል።
ሐዋርያት ትምርታቸውን የተቀበሏቸውን በልጅነት ያከብራሉ ሀብት ሥርየት ይሰጣሉ ያልተቀበሏቸውን በሌጌዎን ይነጻሉ በነፋስ ይሰቅላሉና። ቀላጤም፤ በደለኛ ወታደር ካልገዛው አገር ገብቶ ያልፈላ ያስጠምቃል ያልቦካ ያስጋግራል፤ የተበደለ ድሃ ከንጉሥ ሄዶ ይጮሃል ባዳራሽ ተገኝቶ ቀላጤ ሰጥቶ ይሰደዋል ያ ቀላጤ ባብርሃን የገባውን በጨለማ በፀሐይ የገባውን በዝናም አስወጥቶ የተሰበረ እንጨቱን የተቀዳ ውሀውን ያስመልስለታል። በደለኛ ወታደር ካልገዛው አገር ገብቶ ያልፈላ እንዲያስጠምቅ ያልቦካ እንዲያስጋግር ዲያብሎስ ያልፈጠፈውን ፍጥረት ያልገዛውን ሰውነት ፭ ሽህ ከ፭፻ ዘመን ኃጢአት ሲያሰራ ጣዖት ሲያስመልክ መኖሩን መናገር ነው፡፡ የተበደለ ድሃ ከንጉሥ ሂዶ እንደመጮህ ነቢያት አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ ማለታቸውን መናገር ነው ንጉሥ ባዳራሽ ተገኝቶ ቀላጤ ሰጥቶ እንደመስደድ ቃለ እግዚአብሔር ሰው ሁኖ አሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ሹሞ መስደዱን መናገር ነው። ቀላጤ በብርሃን የገባውን በጨለማ በፀሐይ የገባውን በዝናም እንዲያስወጣ ሐዋርያትም በደዌ የገባውን በታምራት በክህደት የገባውን በትምርት ማስወጣታቸውን መናገር ነው። የተሰበረ እንጨቱን እንዲያስመልስለት በአዳም የሄደውን ልጅነት አስመልሰዋልና ፍንው፤ ወናሁ አነ እፌንወክሙ ከመ አባግዕ ማዕከለ ተኵላት ብሎ እንዲያመጣው ምጥው ከፍንው ይገባል ሃያጅም አለ ይህ ሁሉ ካልሄዱ አይገኝምና።
ቀዳሚ ስምዖን ዘተሰምየ ጴጥሮስ።
አንዱ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለ ስምዖን ነው። (ሐተታ) ጴጥሮስ ማለት መርግ ማለት ነው መርግ ከወደላይ ሲመጣ ያስፈራል። እሱም ሞተ በሥጋ ወሐይወ በመንፈስ እያለ ሲያስተምር ያስፈራልና።
አንድም ሻፎ ደንጊያ ማለት ነው ይህ ሥጋን ከአጥንት ይለያል። እሱም ምዕመናንን ከመናፍቃን ይለያልና።
አንድም ደንጊያ ማለት ነው ይህን የቀን ሐሩር የሌሊት ቊር አይለውጠውም። እሱም በመከራ አይለወጥምና።
አንድም ከዋው ደንጊያ ማለት ነው ያ እየፈጋ ይሄዳል። እሱም ከ፲፩ዱ ስብከት ሁሉ እየገባ ያስተምራልና።
ወእንድርያስ እኊሁ።
ወንድሙ እንድርያስ ነው። (ሐተታ) እንድርያስ ማለት ተባዕ ለመስቀል በኵረ ሐዋርያት ማለት ነው።
                   ******   
፫፡ ወያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
፫፡ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ነው
                   ******   
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
13/08/2011 ዓ.ም

Saturday, April 20, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 70

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ መጻጒዕ።
ምዕራፍ ፱።
                   ******
በእንተ ጽሙም ዘቦቱ ጋኔን
፴፪፡ ወእምዝ አምጽኡ ኀቤሁ ዘጋኔን ፅሙመ ወበሀመ። ማቴዎ ፲፪፥፳፪፡፡ ሉቃ ፲፩፥፲፬።
                   ******   
፴፪፡ ከዚህ በኋላ ጋኔን ድዳ ደንቆሮ ያደረገውን ሰው ይዘው መጡ። ድዳ ደንቆሮ ጋኔን ሲያድርበት ሰውም ድዳ ደንቆሮ ይሆናልና።
አንድም ጽሙም ወበሐም ይላል ድዳ ደንቆሮ ጋኔን ያደረበትን ሰው ይዘው መጡ። ቀድስ ቢሉት አልቀድስም ብሏልና ድዳ አለው። ትእዛዘ እግዚአብሔርን ስማ ቢሉት አልሰማም ብሏልና ደንቆሮ አለው።
                   ******   
፴፫፡ ወወፂኦ ጋኔኑ ነበበ ውእቱ በሐም ወሰምን ውእቱ ጽሙም
                   ******   
፴፫፡ ጋኔኑ በተለየው ጊዜ ድዳ የነበረው ተናገረ ደንቆሮ የነበረው ሰማ።
                   ******   
፴፬፡ ወፈሪሳውያንሰ ይቤሉ በመልአኮሙ ለአጋንንት ያወፅኦሙ ለአጋንንት።
                   ******   
፴፬፡ ፈሪሳውያን ግን ታምራት ያደርጋል ሰው ይሳባል ኦሪት ትጠፋለች ወንጌል ትሰፋለች ብለው የንጉሥን ጭፍራ በንጉሥ ቀላጤ እንዲያስወጡት ከአለቃቸው ከብዔል ዜቡል ተጨዋውቶ ያስወጣቸዋል እንጂ አለዚያ ግን አያስወጣቸውም አሉ። አሁን ለነዚህ ዛሬ አይመልስላቸውም በሚመጣው ጉባዔ ይመልስላቸዋል
                   ******   
በከመ አንሶሰወ ኢየሱስ ውስተ ገሊላ።
፴፭፡ ወአንሶሰወ እግዚእ ኢየሱስ ውስተ ኵሉ አህጉር ወበሐውርት እንዘ ይሜህር በምኵራባቲሆሙ። ማር ፮፥፮።
                   ******   
፴፭፡ በምኵራባቸው እየገባ ሲያስተምር ኖረ
ወይሰብክ ወንጌለ መንግሥት
ጌትነቱን የምትናገር ወንጌልን ሲያስተምር ኖረ። (ሐተታ) እንዳለፈው። ምዕ ፬ ቊ ፳፫፡፡
ወይፈውስ ኵሎ ድውያነ ወኵሎ ሕማመ ዘውስተ ሕዝብ ለዚያው ምልክት በሕዝቡ ዘንድ ያሉ ድውያንን ሁሉ ይፈውስ ነበረ።
                    ******   
፴፮፡ ወርእዮ ብዙኃነ ሰብአ አምህርዎ ወተሣሃሎሙ።
                   ******   
፴፮፡ ብዙ ሰዎችን ባየ ጊዜ አሳዘኑት አዘነላቸው።
እስመ ስሩሃን እሙንቱ።
በፃማ ኦሪት በፃማ ኃጢአት ደክመዋልና።
ወግዱፋን ከመ አባግዕ ዘአልቦ ኖላዊ፡፡
ጠባቂ እንደሌላቸው አባግዕ ሁነዋልና።
                   ******   
፴፯፡ ወእምዝ ይቤሎሙ ለአርዳኢሁ። ሉቃስ ፪፥፪።
                   ******   
፴፯፡ ከዚህ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ አንዲህ አላቸው፤
ማዕረሩሰ ብዙኅ
መከሩ ብዙ ነው
ወገባሩ ኅዳጥ።
ሠራተኛው ግን ጥቂት ነው።
                   ******   
፴፰፡ ሰአልዎ ለበዓለ ማዕረር።
                   ******   
፴፰፡ የመከሩን ባለቤት ለምኑት።
ከመ ይወስክ ገባረ ለማዕረሩ።
ለመከሩ አጫጅ ሠራተኛ ይጨምር ዘንድ።
አንድም ማዕረሩሰ ብዙኀ ሰማዕያኑ ብዙ ናቸሙ። ወገባሩ ኅዳጥ መምሩ አንድ ዮሐንስ ነው ወኅዳጥ ዓሣ እንዲል። ሰአልዎ የመምህርነት ባለቤት እኔን ለምኑኝ።
ከመ ይዌስክ እናንቱን መምራን አድርጌ አስነሣችሁ ዘንድ ወደፊት በሚያመጣው ሹመት አትለምኑ ይል የለም ከዚህ ምነው እንዲህ አለ ቢሉ። ያ ሥጋዊ ነው ይህ ግን መንፈሳዊ ነውና የሚጠቀሙበትም ነውና።
አንድም አስፈቅዶ ለመሾም መከራ በመጣባቸው ጊዜ ተሾሙ ተሾሙ ያለን ለዚህ ነው እንዳይሉ። ምነዋ መከራ ብንቀበል ወደን እንጂ ተሹመነዋል እንዲሉ።
አንድም ማዕረሩ ብዙኅ መጻሕፍተ ነቢያት ንባባቸው ብዙ ነው። ወገባሩ ሕዳጥ ትርጓሜያቸው ጥቂት ነው። ድኅነት አያሰጡም። ሰአልዎ የብሉይ የሐዲስ ባለቤት እኔን ለምኑኝ። ከመ ይወስክ ገባረ። መተርጉማን አድርጌ አስነሣችሁ ዘንድ ድነት እንድታሰጡ አደርጋችሁ ዘንድ፡፡
                   ******   
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
፩፡ ወጸውዖሙ ለ፲ቱ ወ፪ቱ አርዳኢሁ፡፡ ማር ፫፥፲፫፡፡ ሉቃ ፮፥፲፫፡፡ ፱፥፩፡፡
፩፡  አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ጸራቸው፡፡ ማለት ሾማቸው፡፡
                   ******   
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
12/08/2011 ዓ.ም