====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ክርስቲያናዊት ትሕትና፡፡
ምዕራፍ ፲፰።
******
በእንተ ምሳሌ አግብርት ወፈድዮተ ዕዳ።
፳፫፡ ወበእንተዝ እብለክሙ ትመስል መንግሥተ ሰማያት ብእሴ ንጉሠ ዘፈቀደ ይትሀሰቦሙ ለአግብርቲሁ።
******
፳፫፡ ንስሐ የሚገባ ስለሆነ መንግሥተ ሰማያት ሕገ ወንጌል፡ ሕገ ወንጌል ተስፋ፣ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ብላቴኖቹን ሊቆጣጠራቸው የወደደ ንጉሥን ትመስላለች።
******
፳፬፡ ወሶበ አኃዘ ተሀስቦቶሙ አምጽኡ ሎቱ አሐደ ዘይፈድዮ ዕልፈ መካልየ፣
******
፳፬፡ በተቆጣጠራቸው ጊዜ የዕልፍ ወቄት ባለዳ አመጡለት።
******
፳፭፡ ወኃጢኦ ዘይፈድዮ አዘዘ እግዚኡ ይሢጥዎ ምስለ ብእሲቱ ወምስለ ውሉዱ።
******
፳፭፡ የሚክፍለው ቢያጣ ከልጆቹና ከሚስቱ ጋራ ሽጡት ብሎ አዘዘ። በወንጌልስ መሸጥም የለ ተገዝቶ ደመወዝ አውጥቶ ይክፈለኝ ሲል ነው።
******
፳፮፡ ወኵሎ ዘቦ እስከ ይፈዲ።
******
፳፮፡ ዕልፍ ወቄት አስኪከፍል ድረስ።
ወወድቀ እንከ ውእቱ ገብር ወሰገደ ሎቱ ወአስተብቊዖ።
ያ ባሪያ ወድቆ ማለደው።
እንዘ ይብል እግዚኦ ተዓገሠኒ
አቤቱ ታገሠኝ።
ወኵሎ እፈድየከ።
ዕልፍ ወቄት እከፍልሃለሁ ብሎ
******
፳፯፡ ወምህሮ እግዚኡ ለውእቱ ገብር ወዕዳሁኒ ኀደገ ሎቱ፡፡
******
፳፯፡ ለዚያ ባሪያ ጌታው አዘነለት ዕዳውን ሁሉ ተወለት።
******
፳፰፡ ወወጺኦ ውእቱ ገብር ረከበ አሐደ ገብረ እምነ አብያጺሁ ዘይፈድዮ ዕልፈ ዲናረ።
******
፳፰፡ ያ ባሪያ ወጥቶ ከባልንጀሮቹ ወገን የመቶ ወቄት ባለዕዳ አገኘ።
ወአኀዞ ወኀነቆ እንዘ ይብል ሀበኒ ዘትፈድየኒ።
ገንዘቤን ስጠኝ ብሎ አስጨንቆ ያዘው።
******
፳፱፡ ወወድቀ ውእቱ ገብር ታሕተ እገሪሁ ወአስተብቊዖ እንዘ ይብል ተዓገሠኒ።
******
፳፱፡ ያ የጌታ ባርያ ታገሠኝ ማለት ቀን ስጠኝ ብሎ ወድቆ ማለደው፡፡
ወኵሎ እፈድየከ።
ጥቂት ጥቂት እያልሁ ሁሉንም እከፍልሃለሁ፣
******
ወዓበዮ ወሖረ ወሞቅሖ፡
******
፴፡ ብትከፍለኝ ክፈለኝ ያለዚያ አይሆንም ብሎ አሥሮ አጋዘው
እስከ ይፈድዮ፣
እስኪከፍለው ድረስ።
******
፴፩፡ ወርእዮሙ አግብርተ እግዚኡ ዘገብረ ተከዙ ጥቀ፣
******
፴፩፡ የጌታው ባሮች ባልንጀሮቹ ያደረገውን አይተው ፈጽመው አዘኑ፣
ወሐዊሮሙ ነገርዎ ለእግዚኦሙ ኵሎ ዘገብረ
ሂደው ያደረገውን ሁሉ ለጌታቸው ነገሩት ነገሩት፡፡
******
፴፪፡ ወእምዝ ጸውዖ እግዚኡ ኦ ገብር እኵይ ኵሎ ዕዳ ኀደጉ
ለከ።
******
፴፪፡ ከዚህ በኋላ ጌታው ጠርቶ አንት ክፉ ባርያ ዕዳህን ሁሉ ተውሁልህ።
******
፴፫፡ እስመ አስተብቋዕከኒ።
******
፴፫፡ ማልደኸኛልና ስለ ማለድኸኝ
አኮሁ መፍትው አንተሂ ትምሀር ውእተ ገብረ ቢጸከ በከመ አነ መሀርኩከ።
እኔ ዕልፍ ወቄት እንደተውኩልህ አንተስ ልትተው አይገባህም ነበርን።
******
፴፬፡ ወተምዓ እግዚኡ ወመጠዎሙ ለእለ ይሣቅይዎ።
******
፴፬፡ ጌታው ተቆጥቶ እሱ ለሰው ካላዘነ ብሎ መከራ ሥቃይ ለሚያጸኑበት ሰጠው።
እስከ አመ ይሤልጥ ኵሎ ዘይፈድዮ።
ዕልፍ ወቄት አስኪከፍለው ድረስ።
******
፴፭፡ ከማሁኬ አቡየኒ ሰማያዊ ይገብር ለክሙ እመ ኢኃደግሙ አበሳሆሙ ለቢጽክሙ እምኵሉ ልብክሙ።
******
፴፭፡ እንደዚህም ሁሉ የወንድዎቻችሁን ኃጢአት በፍጹም ልቡናችሁ ይቅር ካላላችሁ ሰማያዊ አባቴም እንዲህ ያደርግባችኋል።
አንድም ትመስል መንግሥተ ሰማያት ብለህ መልስ። መንግሥተ ሰማያት አብ መላአክትን ሊቆጣጠራቸው የወደደ ንጉሥን ትመስላለች አለ እሱ ነው ማለት ነው።
ወሶበ አኀዘ ተሀስቦቶሙ።
በተቆጣጠራቸው ጊዜ ፍጹም ኃጢአት የሠራ አዳምን አመጡለት።
ወኃጢኦ ዘይፈደዮ።
ሃይማኖት ምግባር ቢያጣበት።
አዘዘ ይሢጥዎ
በእሱ በሔዋን በልጆቹ ሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስን ፈረደባቸው። በአዳም ሁሉን መናገር ነው፡፡
አንድም መምህረ ንስሐ ነው፡፡
አዘዘ ይሢጥዎ
በሕዋሳቱ ደዌያትን ፈረደበት
ወኵሎ ዘቦ
ቀኖናውን እስኪፈጽም ድረስ።
ወወድቀ ወአስተብቊዖ
በድዬሃለሁ ይቅር በለኝ።
ወኵሎ እፈድየከ
ቀኖናዬን እፈጽማለሁ አለው።
ወምህሮ
አዘነለት ኃጢአቱን አስተስረየለት፡፡
ወወፂኦ
ኃጢአቱ ከተሰረየለት በኋላ ከሕዝቡ አንድ ተነሳሂ አገኘ።
ወአኃዞ ወሐነቆ
መጽሐፍ ያዘዘውን ፈጽም ብሎ አስጨንቆ ያዘው።
ወወድቀ ወአስተብቊዖ
ቀኖናዬን ልፈጽም ብሎ ማለደው፡፡
ወአበዮ ወሞቅሖ
ብትፈጽም ፈጽም አለዚያ አይሆንም ብሎ አወገዘው።
እስከ ይፈደዮ
ቀኖናውን እስኪፈጽም ድረስ።
ወርእዮሙ አብያጺሁ
መላእክት አይተው ፈጽመው አዘኑ ሰው ለሰው እንዲህ ይጨክናል ብለው።
ወሐዊሮሙ ነገርዎ
ሂደው የሠራውን ሥራ ሁሉ ለጌታቸው ነገሩት።
(ሐተታ) መንገሩስ የለም የነገሩት አውቆ ሥራ እንዲሠራ አውቆ ሥራ መሥራቱን መናገር ነው።
ወእምዝ ጸውዖ
ከዚህ በኋላ በደዌ ጸራው።
ወይቤሎ
አንተ ክፉ ቄስ እኔ ኃጢአትህን ሁሉ አስተሰረይኩልህ።
እስመ አስተብቋዕከኒ፡፡
ማልደኸኛልና ስለማለድኸኝ።
አኮሁ መፍትው
እኔ ይቅር እንዳልኩህ አንተስ የወንድምህን ኃጢአት ልታስተሰርይለት አይገባሕምን። ተመየጥ አንተ ወአነ ተወከፍኩ ህየንቴከ ሞተ በከመ ተወክፈ ክርስቶስ ሞተ ህየንቴየ ወህየንተ ኵሎሙ ልትለው አይገባህም ነበር አለው።
ወተምዓ ወመጠዎ
ፈርዶ መከራ ለሚያጸኑበት ለደዌያት ሰጠው።
እስከ ይፈዲ
ቀኖናውን እስኪፈጽም ድረስ።
ወከማሁኬ
የወንድማችሁን ኃጢአት በፍጹም ልቡናችሁ ይቅር ካላላችሁ ሰማያዊ አባታትሁ አሁን እንደተናገርሁት ያደርግባችኋል።
******
በእንተ ዘተግኅሠ ኢየሱስ እምኢየሩሳሌም።
ምዕራፍ ፲፱፡፡
፩፡ ወሶበ ፈጸመ እግዚእ ኢየሱስ ተንሥአ እምገሊላ ወሖረ ወበጽሐ ውስተ ብሔረ ይሁዳ ማዕዶተ ዮርዳኖስ። ማር ፲፥፩፡፡
፩፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ነገር አስተምሮ ከፈጸመ በኋላ ከገሊላ ወጥቶ የዮርዳኖስ ማዶ ወደሚሆን ወደምድረ ይሁዳ ደረሰ።
******
ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
18/09/2011 ዓ.ም
Saturday, May 25, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 102
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 101
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ክርስቲያናዊት ትሕትና፡፡
ምዕራፍ ፲፰።
******
በእንተ ዘከመ ይደልዎሙ ለአኃው ተገሥጾ።
፲፭፡ ወእመኒ አበሰ ለከ እኁከ ሑር ወገሥፆ ለባሕቲትከ፡፡ ዘሌዋ ፲፱፥፲፯፡፡ ሲራ ፲፱፥፲፫፡፡ ሉቃ ፲፯፥፫፡፡ ያዕ ፭፥፲፱፡፡
******
፲፭፡ ወንድምህ ቢበድልህ በብቻህ ሁነህ በብቻው አድርገህ ለባሕቲትከ ለባሕቲቱ ለብቻህ ሁነህ ለብቻው አድርገህ ብቻህን ሁነህ ብቻውን አድርገህ ምከረው።
ወእመ ሰምዓከ ረባሕኮ ለእኁከ።
የተቀበለህ እንደሆነ ረባኸው ጠቀምኸው።
******
፲፮፡ ወእመሰ ኢሰምዓከ ንሣእ ምስሌከ በዳግም አሐደ። ዘዳ ፲፥፮፡፡ ዮሐ ፰፥፲፯፡፡ ፪፡ቆሮ ፲፫፥፩፡፡ ዕብ ፲፥፳፰።
******
፲፮፡ ባይቀበልህሀ ግን በሁለተኛው አንድ ሰው ጨምረህ ምከረው።
አው ፪ተ።
እናንተን ባይቀበል ሁለት ሰው ጩጨምረህ አንተ ሦስተኛ ሁነህ ምከረው።
እስመ በአፈ ፪ቱ ወ፫ቱ ሰማዕት ይቀውም ኵሉ ነገር።
በሁለት ምስክር ነገር ይጸናልና።
ንሣእ አሐደ
በሦስት ምስክር ነገር ይጸናልና፡፡
አንድም በአምስት ምስክር ነገር ይጸናልና፡፡ ንሣአ ፪ተ አው ፫ተ።
******
፲፯፡ ወእመሰ ኢሰምዖሙ ሎሙሂ ንግራ ለቤተ ክርስቲያን። ፩፡ቆሮ ፭፥፱፡፡ ፪፡ተሰሎ ፫፥፲፫፡፡
******
፲፯፡ እሳቸውንም ባይቀበል ንግሩ ለጉባዔ ይላል የፍርድ መጣፍ ባንድ ደወል ለሚሰበሰቡ ንገሩ እኒያን ባይቀበል ለቤተ ክርስቲያን ንገሩበት።
ወእመሰ ለቤተ ክርስቲያን ኢሰምዓ ይኩን ከመ አረማዊ ወመጸብሐዊ።
ቤተ ክርስቲያንንም ባይሰማት እንደ አረማዊ እንደ መጸብሐዊ ይሁን ማለት ይለይ።
(ሐተታ) ወንድሙን ቢበድል እግዚአብሔርን የካደ ይመስል ይለይ ማለቱ ስለምነው ቢሉ። ወንድሙን ከበደለ ከሥጋው ከደሙ ይከለከላል ከሥጋው ከደሙ ከተከለከለ እንደ አረማዊ እንደ መጸብሐዊ መሆኑ ነውና፡፡
አንድም የሚያየውን ወንድሙን መበደሉ እግዚአብሔርን መበደሉ ነውና።
******
፲፰፡ አማን እብለክሙ ዘአሠርክሙ በምድር ይኩን እሱረ በሰማያት። ዮሐ ፳፥፳፫።
******
፲፰፡ ከምድራውያን ነገሥታት ከሌዋውያን ካህናት ወገን ያይደለን መለየቱ እንደምን ይሆናል ትሉኝ እንደሆነ በምድር ያሠራችሁት በሰማይ የታሰረ እንዲሆን።
ወዘፈታሕክሙ በምድር ይከውን ፍቱሐ በሰማያት።
በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ እንዲሆን በእውነት እነግራችኋለሁ። እንዳለፈው ም፲፮ ቊጥር ፲፱።
******
፲፱፡ ወዓዲ እብለክሙ ለእመ ኃብሩ ፪ አው ፫ እምኔክሙ በውስተ ምድር በእንተ ኵሉ ግብር ዘሰአሉ ይትገበር ሎሙ በኃበ አቡየ ዘበሰማያት።
******
፲፱፡ ያውስ ቢሆን ጥቂት ነን ብዙ አይደለን መለየቱ እንደምን ይሆንልናል ትሉኝ እንደሆነ ከእናንተ ወገን ስለሚሹት ነገር በዚህ ዓለም ሁለቱ ወይም ሦስቱ አንድ ቢሆኑ በሰማይ አባቴ ዘንድ የሚሹት ነገር ይደረግላቸዋል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡
******
፳፡ እስመ ኀበ ሀለዉ ፪ቱ ወ፫ቱ ጉቡዓነ በስምየ ህየ እሄሉ አነ ማዕከሎሙ።
******
፳፡ ሁለቱ ሦስቱ በስሜ አምነው አንድ ቢሆኑ አንድ በሆኑበት እኖራለሁ ማለት አድሬባቸው እኖራለሁና።
(ሐተታ) ሠለስቱ የተባሉ አንባቢ ተርጓሜ መጽሐፍ ናቸው።
አንድም ናዛዚ ተናዛዚ ኄር ላእክ ናቸው።
አንድም ንጽሐ ሥጋ ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ናቸው። ሃይማኖት ትውክልት ተፋቅሮ ናቸው ።
******
፳፩፡ ወእምዝ ቀርበ ጴጥሮስ ወይቤሎ እግዚኦ ሚመጠነ አመ አበሰ ሊተ እኁየ እኅድግ ሎቱ፡፡ ሉቃ ፲፯፥፬፡፡
******
፳፩፡ ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ አቤቱ ወንድሜ ምን ያህል ቢበድለኝ ይቅር ልበለው።
እስከ ስብዕኑ
እስከ ሰባት ድረስ ነውን አለው፡፡
******
፳፪፡ ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ኢይብለከ እስከ ስብዕ።
******
፳፪፡ እስከ ሰባት አልልህም
አላ እስከ ሰብዓ በበስብዕ
ሰባቱን አንድ ሰባቱን አንድ እያልክ እስክ ሰባ ነው እንጂ
አንድም እስከ ስብዕ በበሰብዓ
ሰባውን አንድ እየልክ እስከ ሰባት ነው እንጂ አለው።
******
በእንተ ምሳሌ አግብርት ወፈድዮተ ዕዳ።
፳፫፡ ወበእንተዝ እብለክሙ ትመስል መንግሥተ ሰማያት ብእሴ ንጉሠ ዘፈቀደ ይትሀሰቦሙ ለአግብርቲሁ።
፳፫፡ ንስሐ የሚገባ ስለሆነ መንግሥተ ሰማያት ሕገ ወንጌል፡ ሕገ ወንጌል ተስፋ፣ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ብላቴኖቹን ሊቆጣጠራቸው የወደደ ንጉሥን ትመስላለች።
******
ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
17/09/2011 ዓ.ም
Friday, May 24, 2019
ወንጌል ቅዱስ ክፍል 100
====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በእንተ ክርስቲያናዊት ትሕትና፡፡
ምዕራፍ ፲፰።
******
፩፡ ወበይእቲ ሰዓት ቀርቡ ኀቤሁ አርዳኢሁ ለእግዚእ ኢየሱስ
እንዘ ይብሉ መኑ እንጋ የዓቢ በመንግሥተ ሰማያት። ማር ፱፥፴፫፡፡ ሉቃ ፱፥፵፮፡፡ ማቴ ፲፱፥፲፬፡፡
******
፩፡ ከዚያ ብፅዓን ሰጠው ከዚህ ገበረለት ሾመው እንጂ ሾመው ተባብለዋል። በዚያች ሰዓት ደቀ መዛሙርቱ ቀርበው በመንግሥተ ሰማይ በላይ የሚሆን ማነው አሉት፡፡
******
፪፡ ወጸውዓ ሕፃነ ወአቀመ ማዕከሎሙ።
******
፪፡ ብላቴና ጠርቶ አቆመው።
******
፫፡ ወይቤ አማን እብለክሙ እመ ኢተመየጥክሙ ዝንቱ ሕፃን ኢትበውኡ ውስተ መንግሥተ ሰማያት። ፩፡ቆሮ ፲፬፥፳፡፡
******
፫፡ ተመልሳችሁ ከየውሃት ጠባይዓዊ ደርሳችሁ እንደዚህ ሕፃን ካልሆናችሁ መንግሥተ ሰማይ እንዳትገቡ በእውነት እነግራችኋለሁ።
******
፬፡ ወዘአትሐተ ርእሶ ከመ ዝንቱ ሕፃን ውእቱ የዓቢ በመንግሥተ ሰማያት።
******
፬፡ በመካከላቸው እንደዚህ ሕፃን ሁኖ ራሱን ያዋረደ የመንግሥተ ሰማይ ባለቤት ይሆናል። ይህም ትሕትና የሚያስተምርበት ሕፃን አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ነው። በአንጾኪያ የጴጥሮስ ሦስተኛ ሁኖ ተሹማል።
******
፭፡ ወዘሂ ተወክፈ ፩ደ ሕፃነ ዘከመዝ በስምየ ኪያየ ተወክፈ
******
፭፡ እንደዚህ ሕፃን የሆነውን በእኔ ስም የተቀበለ እኔን ተቀበለ ማለት እኔ አድርበታለሁ።
******
በእንተ ዘተናገረ ኢየሱስ በላዕለ ዕቅፍት።
ወዘሂ አስሐቶ ለ፩ዱ እምእሉ ንዑሳን እለ የአምኑ ብየ ይኄይሶ ከመ ይዕሥሩ በክሣዱ ማኅረፀ አድግ ወያስጥምዎ ውስተ ልጐተ ባሕር።
******
፮፡ በእኔ ከአመኑ ምዕመናን አንዱን ያሳተ አህያ በመዘውር የሚፈጭባትን ወፍጮ ከአንገቱ አሥሮ ከጥልቅ ባሕር ቢያሰጥሙት ይሻለዋል።
አንድም ጽኑ ቀኖና ሰጥተው በአንብዓ ንስሐ ቢያሰጥሙት ይሻለዋል።
******
፯፡ አሌ ሎቱ ለዓለም እመንሱት ዘይመጽእ።
******
፯፡ ከሚመጣው መከራ የተነሣ ለሰው ሁሉ ወዮለት።
እስመ ግብር ይመጽእ መንሱት
መከራ ግድ ይመጣልና።
ወባሕቱ አሌ ሎቱ ለውእቱ ብእሲ ዘያመጽኣ ለመንሱት።
ነገር ግን ዋዛ ፈዛዛ ተጫውቶ መከራን ለሚያመጣት ለይሁዳ ወዮለት።
******
፰፡ ወእመኒ እዴከ አው እግርከ ታስሕተከ ምትራ ወግድፋ እምላዕሌከ። ማቴ ፭፥፴፡፡ ማር ፱፥ሣ፪።
******
፰፡ እጅህም ብትሆን ወይም እግርህ ብታስትህ ከአንተ ቈርጠህ ጣላት።
እስመ ይኄይሰከ ትባእ ውስተ ሕይወት ሐንካሳከ ወጽውሰከ እምእንዘ ብከ ፪ አዕዳው ወ፪ አእጋር ትትወደይ ውስተ እሳት ዘለዓለም።
ሁለት እጅ ሁለት እግር ኑሮህ ወደ ዘለዓለም እሳት ስትገባ አንካሳ ልምሾ ሁነህ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሸልሃልና።
******
፱፡ ወእመሂ ዓይንከ ታስሕተከ ምልሓ ወአውጽኣ እምላዕሌከ
******
፱፡ ዓይንህ ብታስትህ አውጥተህ ጣላት።
******
እስመ ይኄይሰከ ነቋረከ ትባዕ ውስተ ሕይወት እምትባዕ ምስለ ፪ሆን አዕይንቲከ ውስተ እሳተ ገሃነም።
ሁለት ዓይን ኑሮህ ወደ ገሃነመ እሳት ከምትገባ አንድ ዓይን ኑሮህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሸልሃልና፡፡
አንድም ወእመሂ ዓይንከ ብለህ መልስ፡፡ ኤጲስ ቆጶስህን ብትነቅፈው ሻረው፡፡ እስመ ይኄይሰከ የነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሹመህ ኑረህ ኋላ ገሃነመ እሳት ከምትገባ የነቀፍኸውን ኤጲስ ቆጶስ ሽረህ ኑረህ ኋላ መንግሥተ ሰማይ ብትገባ ይሻልሃልና፡፡
******
፲፡ ዑቁ ኢታስተኃቅርዎሙ ለ፩ እምእሉ ንዑሳን፡፡ መዝ ፴፫፥፯፡፡
******
፲፡ ከአመኑ ምዕመናን አንዱን እንዳትንቁ እንዳታቃልሉ አስተውሉ፡፡
እብለክሙ ከመ መላእክቲሆሙ በሰማያት ወትረ ይሬእዩ ገጾ ለአቡየ ዘበሰማያት።
መላአክት ዑቃቤዎቻቸው ያባቴን ፊት ዘወትር ያያሉ ማለት መላእክተ ዑቃቤዎቻቸው በባለሟልነት እንዳሉ እነግራችኋለሁ እንዳይቀስፏችሁ ማለት ነው።
አንድም መላአክተ ዑቃቤዎቻቸው በባለሟልነት እንዳሉ እሳቸውም በባለሟልነት እንዳሉ እነግራችኋለሁ እንዳያስፈርዱባችሁ ማለት ነው።
******
በእንተ በግዕት ዘተሐጕለት።
፲፩፡ እስመ መጽአ ወልደ እጓለ እመሕያው ይኅሥሥ ወያድኅን ዘተኃጕለ። ሉቃ ፲፱፥፲።
******
፲፩፡ ወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስ የጠፋውን ሊሻ የተጐዳውን ሊያድን ሰው ሁኑዋልና።
******
፲፪፡ ምንተ ትብሉ። ሉቃ ፲፫፥፬።
******
፲፪፡ አንቀጸ ንስሐ ነው ምን ትፈርዳላችሁ።
እመቦ ብእሲ ዘቦቱ ፻ አባግዕ።
መቶ በግ ያለው ሰው ቢኖር
ወእመ ተገድፎ ፩ እምኔሆሙ፡፡
ከመቶው አንዱ ቢጠፋበት።
አኮሁ የኃድግ ፺ወ፱ተ ውስተ ገዳም።
ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ።
ወየሐውር ይኅሥሥ ዘተገድፎ
የጠፋበትን ሊፈልግ ይሄድ የለምን።
******
፲፫፡ ወእምከመ ረከቦ አማን እብለክሙ ከመ ይትፌሣሕ በእንቲአሁ ፈድፋደ እም ፺ወ፱ እለ ኢተገድፉ።
******
፲፫፡ ያገኘው እንደሆነ ካልጠፉት ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ ጠፍቶ በተገኘው ደስ ይለዋል ብዬ ደስ እንዲለው በእውነት እነግራችኋለሁ።
******
፲፬፡ ከማሁኬ ኢይፈቅድ አቡየኒ ዘበሰማያት ከመ ይትኃጐል ፩ዱ እምእሉ ንዑሳን።
******
፲፬፡ እንደዚህም ሁሉ ሰማያዊ አባቴ ከተነሣሕያን አንዱ ሊጐዳ አይወድም።
አንድም ምንተ ትብሉ ብለህ መልስ። መቶ በጎች የተባሉ መቶ ነገደ መላእክት ናቸው ከመቶው አንዱ ዲያብሎስ ቢወጣ በሱ ስፍራ አዳም ቢገባ አዳም ቢወጣ አኮሁ የኃድግ ባሕርየ መላእክትን ትቶ ባሕርየ አዳምን ገንዘብ ማድረጉን መናገር ነው። ኢነሥኦ ለዘነሥኦ እመላእክት ዘእንበለ ዳዕሙ እምዘርዓ አብርሃም እንዲል። ወእምከመ ረከበ አዳምን ንስሐ ገብቶ ቢያገኘው አማን እብለክሙ ንስሐ ከማያሻቸው ከመላእክት ይልቅ ንስሐ በሚያሻው በአዳም መመለስ ደስ ይለዋል ብዬ በእውነት እነግራችኋለሁ።
ከማሁኬ ኢይፈቅድ አቡየኒ ዘበሰማያት ከመ ይትኃጐል ፩ዱ እምእሉ ንዑሳን፡፡
አሁን እንደ ተናገርነው ሰማያዊ አባቴ ከተነሳሕያን አንዱ ሊጐዳ አይወድም።
******
በእንተ ዘከመ ይደልዎሙ ለአኃው ተገሥጾ\።
፲፭፡ ወእመኒ አበሰ ለከ እኁከ ሑር ወገሥፆ ለባሕቲትከ፡፡ ዘሌዋ ፲፱፥፲፯፡፡ ሲራ ፲፱፥፲፫፡፡ ሉቃ ፲፯፥፫፡፡ ያዕ ፭፥፲፱፡፡
******
፲፭፡ ወንድምህ ቢበድልህ በብቻህ ሁነህ በብቻው አድርገህ ለባሕቲትከ ለባሕቲቱ ለብቻህ ሁነህ ለብቻው አድርገህ ብቻህን ሁነህ ብቻውን አድርገህ ምከረው። ይቆየን፡፡
**********
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
16/09/2011 ዓ.ም