ነሐሴ 21/2009
ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ፣ ኢትዮጵያ
=============================================
መረጃዎችን ለማግኘት (
facebook.com/beyenemlkm እና/ወይም facebook.com/tomarthetewahido ) ላይክ ያድርጉ፡፡
===================================================
ዛሬ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም በዓል ቀን በደብረ ማርቆስ ከተማ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ላስቀደሱ ምእመናን ነሐሴ 19/2009 ዓ.ም የለጠፍሁትን ጽሑፍ ፕሪንት አድርገው መድረክ ላይ እያነበቡ ለምእመናን ግንዛቤ ሲፈጥሩ ውለዋል፡፡ ይህ ጽሑፍ ዋና መልእክቱ መድረክ ላይ ተጣሞ እንደተላለፈው ያለ አይደለም፡፡ እኔ የጻፍሁት ስለራሴ ብቻ የራሴን ሃሳብ ይዠ ነው፡፡ የራሴን ሃሳብ ይዠ ይሁን እንጅ እናት ቤተክርስቲያን እንድትሰደብ እና እውነተኛ ካህናት እንዲጠሉ አላደረግሁም ወደፊትም አላደርግም፡፡ “አክሊሌን ተንጠልጥሎ አየሁት” የሚለው ጽሑፌ ላይ በዋናነት ማንሣት የፈለግሁት ኅሊናየ ውስጥ የሚመላለሰውን ጥያቄየን ነው፡፡ ማሰቀደስ እፈልጋለሁ ግን የእምነት ልዩነት ያላቸው ካህናት አብረው እንደሚቀድሱ ሳስብ ኅሊናየ እረፍት ያጣል ታዲያ እንዴት ላስቀድስ የሚል ነው፡፡ ታዲያ ለዚህ እኮ ተገቢ መልስ እንደአባትነታችሁ ልትሰጡኝ ይገባ ነበር እንጅ እንዲህ መድረክ ላይ አጀንዳ አድርጋችሁ ልታነሡኝ አይገባም ነበር፡፡ ሊቃውንቱ ተሰብስበው ሊፈቱት የሚገባውን ጥያቄ ለምን አጣማችሁ መድረክ ላይ እንዳመጣችሁት ባላውቅም እኔ ግን ኅሊናየን የሚያሳርፍልኝ መልስ እሻለሁ፡፡

እኔ የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆኔን ስሰማ የእኔን ገጽ የማይከታተል
ካህን የለም ማለት ነው እንዴ አልኩኝ፡፡ ይህን ያህል ትልቅ አጀንዳ የምሆን ሰው አይደለሁም እኮ፡፡ የሚከታተለኝም ሰው ይህን ያህል
ብዙ የሚባል ስላልሆነ ስጋታችሁ ልሆን እንደማልችል ይገባኛል፡፡ ስለዚህ ወደ መፍትሔው ብናተኩር መልካም ይመስለኛል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ
ግን እኔን ወደ በረከት እንደምትመሩኝ አልጠራጠርም፡፡ ሰማእትነትም አለና፡፡ እዚሁ በመካከላችሁ ስላለሁኝ የሚመጣውን ማንኛውንም
ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ምክንያቱም ከውስጤ ፍቄ የማላወጣው ተዋሕዶ እምነቴ ያስገድደኛልና፡፡
No comments:
Post a Comment