Wednesday, July 6, 2016

“ጵጵስና ሹሙኝ”

© መልካሙ በየነ
ሰኔ 29/2008 ዓ.ም
ደብረማርቆስ፣ ኢትዮጵያ

በቤተክርስቲያኛችን የማዕረግ ደረጃ ጵጵስና ትልቁ ነው፡፡ ቀደምት አባቶቻችን ወይም እረኞቻችን ምን ዓይነት ምግባር እና ሃይማኖት ሊኖራቸው እንደሚገባ ጽፈውልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሥልጣን ሹመት የለም ምክንያቱም እረኛ ጠባቂ ልንሆን እንጅ ልንገዛቸው አልተመረጥንምና እያሉ ራሳቸውን በትህትና ይገዙ ነበር፡፡ ቀደምቱማ ለቀሚሳቸው ኪስ የለውም ነበር፤ ቀደምቱማ በእጃቸው ከመስቀል ውጭ አይጨብጡም ነበር፤ ቀደምቱማ ለእግራቸው ጫማ አይሉም ነበር፤ ቀደምቱማ ለጉዟቸው አውሮፕላን መኪና እና ባቡር አይሉም ነበር ሲያሻቸው ደመና ጠቅሰው ሲያሻቸው ደግሞ እግዚአብሔር በፈጠረላቸው እግራቸው ይሄዳሉና፤ ቀደምቱማ ለእግዚአብሔር ብቻ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ ነበሩ፤ ቀደምቱማ ብህትውናን ገንዘባቸው ያደረጉ ነበሩ፤ ቀድምቱማ አስኬማቸውን አክሊለ ሶክ ነው ይሉ ነበር፤ ቀደምቱማ ለሐገር ለወገን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር፤ ቀደምቱማ ይመክሩ ያስተምሩ ነበር፤ ቀደምቱማ ለእምነታቸው በመጋዝ ይሰነጠቁ ነበር፤ ቀደምቱማ ለማዕረጉ ብቁ አይደለሁም ይሉ ነበር፤ ቀደምቱማ በመመረጣቸው ያለቅሱ ያነቡ ነበር፤ ቀደምቱማ መልካም እረኛ የምሆነው እንዴት ነው ብለው ይጨነቁ ነበር ቀ…ደ…ም…ቱ…ማ…!...!...!
ዛሬ ታሪኩ ሁሉ ተለውጧል፡፡ የቀደምት አባቶቻችን ለዛቸው ጣዕማቸው ፍቅራቸው ሊገባንና ልንቀምሰው አልቻልንም፡፡ የዛሬዎቹ ደግሞ እጅግ ተቃራኒዎች ናቸው፡፡ የዛሬዎቹማ ለቀሚሳቸው ሠላሳ ኪስ ያላቸው ናቸው፡፡ ኪሶቻቸው ደግሞ ቤተሰቦቻቸው ጭምር ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ሀብትና ንብረት በማይጠረቃ ኪሳቸው ለማጠራቀም ጵጵስና ካልተሾምሁ አለቀላችሁ እያሉ የሚደነፉ ናቸው፡፡ የዛሬዎቹማ በእጃቸው መስቀል አይጨብጡም የሚጨብጡት ሌላ ነገር አላቸው፡፡ ሲፈልጉ የመንግሥትን እጅ ይጨብጣሉ፣ ሲፈልጉ የመናፍቃኑን እጅ ይጨብጣሉ፣ ሲፈልጉም የዘራፊዎችን እጅ ይጨብጣሉ፡፡ ዛሬ የሰማነው ነገር እሱ ነው መንግሥት እገሌ ጵጵስና ካልተሾመ ሌላ ሾማችሁ ብትልኩልን አንቀበለውም ብሎ ደብዳቤ እያዘነበ ነው፡፡ ታዲያ የዚች ቤተክርስቲያን መሪዎቿ የመንግሥት አካላት ሲሆኑ ዝም ልንል ይገባናልን፡፡ የዛሬዎቹማ ለእግራቸው ጫማ ብቻ ሳይሆን የወርቅ ጫማም ቢሆን ይመርጣሉ ምክንያቱም ገንዘብ አላቸዋ፡፡ እነርሱ የመዘበሩት የቤተክርስቲያን ገንዘብ እንኳን ለእነርሱ እግር ብቻ ለዘመዶቻቸውም ሁሉ የወርቅ ጫማ ይገዛ አይደል እንዴ፡፡ የዛሬዎቹማ ለጉዟቸው አውሮፕላን መኪና እና ባቡር ካልሆነ በእግራቸው አይሞክሯትም ደመና ጠቅሰው እንዳይሄዱ ደግሞ በየትኛው ቅድስና ደመና ይታዘዛል፡፡ በእግራቸውም እንዳይሞክሩት የምታውቁት ነው ዝሆን እስኪያካክሉ ድረስ በቤተ ክርስቲያኗ ገንዘብ ደልበዋል፡፡ እንግዲህ ከዚህ የበለጠ ለመድለብ ነው ጵጵስና ሹሙን እያሉ ራሳቸውን ለዚህ ማዕረግ ብቁ ያደረጉ የሚመስሉት፡፡ የዛሬዎቹማ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡት ለእግዚአብሔር ሳይሆን ለገንዘብ እና ለቅምጦቻቸው ነው፡፡ የማይገባኝ ነገር አለ ሰው የፍትወቱን ጾር መታገስ ካልቻለ ለምን ህጋዊ ሆኖ አግብቶ ልጅ ወልዶ ልጆቹን እየሳመ አይኖርም፡፡ ምንኩስና እኮ ዝም ብሎ ተዘሎ የሚገባበት ባህር አይደለም፡፡ የምንኩስናውን ቆብ ከጫኑ በኋላ አግብተው በግልጽ መኖር ስለሚከብዳቸው ቤት ተከራይተው ያው ኃጢአቱን ይሠሩታል፡፡ በዚህ ግብራቸው ህጋዊ ባለትዳሮችን ሁሉ ትዳር የሚያፈርሱ በዝተዋል፡፡ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ናቸው ዛሬ ጵጵስና ካልሾማችሁን እያሉ በገንዘብም በመንግሥትም በማስፈራራትም ተመዝግበው የምናገኛቸው፡፡ የዛሬዎቹማ ብህትውናን ገንዘባቸው ማድረግ ሳይሆን ብህትውና ምን እንደሆነም ትርጉሙ አይገባቸውም፡፡ መቼም አስኬማው ብቻ አያመነኩስም መነኩሴ ያስመስለን እንደሆነ እንጅ፡፡ ራሳችንን ማመንኮስ ካልቻልን ምን ዋጋ አለው “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ” ይሆንብናል ነገሩ፡፡ ለቅምጦቻቸው ያስቡ ወይስ ለእግዚአብሔር ቤት ያስቡ፣ በድብቅ ለወለዷቸው ልጆች ያስቡ ወይስ ለእኛ ያስቡ፡፡ አስቸጋሪ ነው ይህንን ጉድ ይዘው ዛሬ ጵጵስና ቢሾሙ “ጳጳሱ እንዲህ አደረጉ” እየተባለ ቤተክርስቲያናችን ባለቤት አልባ ስትሆን ምንኛ እንደሚጎዳን አስቡት፡፡ የዛሬዎቹማ አስኬማቸው አክሊለ ሶክ ሳይሆን አክሊለ ብር ሆኖላቸዋል፡፡ ጃንጥላ ዘቅዝቀው ብር ሲሰበስቡ ጃንጥላው ከሞላባቸው ቀጣይ ዘቅዝቀው የሚለምኑበት አስኬማቸው ነው፡፡ የእንጦንስና የመቃርስ አስኬማ የብር መለመኛ ሲሆን ምንኛ ያስለቅሳል፡፡ እነዚህ አስኬማ ዘቅዝቀው የሚለምኑት ሰዎች ዛሬ ጵጵስና ካልሾማችሁን አለቀላችሁ እያሉ እየዛቱ ነው፡፡ የዛሬዎቹማ ለሐገር ለወገን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው የሚሰጡ ሳይሆኑ አንተን ለሞት አሳልፈው የሚሰጡ ጨካኞች ናቸው፡፡ ለጠላት አውጥተው የሚወረውሩ እረኛ ነን የሚሉ ግን እረኛ መሆን የማይችሉ ተኩላዎች ናቸው፡፡ እነዚህ በጥቂቱ ያልታመኑት ዛሬ በብዙው ላይ እንዴት ይታመናሉ ተብሎ ወደ ጵጵስና ይመጣሉ፡፡ የዛሬዎቹማ እንዳይመክሩ ራሳቸውንም መምከር የማይችሉ ናቸው እንዳያስተምሩም የተማሩት ነገር የላቸውም፡፡ ከማስተማር ይልቅ ብጥብጥና ንትርክ በመፍጠር ህዝቡን መከፋፈል የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ይሆናል፡፡ ሌሎች እንዳያስተምሩም መድረኩን አይሰጡም፡፡ የዛሬዎቹማ ለእምነታቸው በመጋዝ እስከመሰንጠቅ የሚያደርስ ጥንካሬ የላቸውም፡፡ እንዲያውም እነርሱ ራሳቸው በመጋዝ ይሰነጥቁ እንደሆነ እንጅ ለእምነታቸው ዋጋ የሚከፍሉ አይደሉም፡፡ ከመንግሥት ጎን ተለጥፈው የመንግሥትን ፖሊሲ አስፈጻሚዎች እስኪመስሉ ድረስ እንደዚያ ናቸው፡፡ እነዚህ ታዲያ ጵጵስና ቢመረጡ የመንግሥትን ወይስ የቤተክርስቲያንን ሥራ ነው የሚሠሩ፡፡ የዛሬዎቹማ ለማዕረጉ ብቁ ነን ምረጡን እያሉ እንደ ፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ ጀምረዋል፡፡ የራሳቸውን ደጋፊና አቀንቃኝም አደራጅተዋል፡፡ ከተመረጡ በኋላ ጵጵስናውን ከተሾሙ በኋላ እነዚህን ደጋፊዎች የየደብሩ አስተዳዳሪዎች ያደርጓቸው ይሆን? አምላክ ይወቀው ሁሉንም፡፡ የዛሬዎቹማ ባለመመረጣቸው ያለቅሱ ያነቡ እንደሆነ እንጅ በመመረጣቸው አያለቅሱም አያነቡም፡፡ በእውነት በኅሊና ላለ ሰው ራስን መምራት ራስን ማስተዳደር ራስን ለእግዚአብሔር መስጠት አስቸጋሪ በሆነበት በዚህ ዘመን ለሌሎች እረኛ መሆን አይከብድምን? በጣም ከባድ እኮ ነው፡፡ ለዚህም ነው አንዳንድ ጥቂት የጥንት አባቶቻችንን ትህትና የተላበሱት ዛሬም ሲመረጡ እኔ ለእረኝነት ብቁ አይደለሁም የሚሉት፡፡ የዛሬዎቹማ መልካም እረኛ ለመሆን ሳይሆን ጥሩ አሳዳጅ ለመሆን ራሳቸውን ያዘጋጁ ናቸው፡፡ እነዚህን ይመስላሉ ጵጵስና ምረጡኝ እያሉ ቅስቀሳቸውን ያጠናከሩት፡፡ የ…ዛ…ሬ…ዎ…ቹ…ማ…!...!...!
እኔ በጣም የሚገርመኝ አንድ አሠራር አለ፡፡ መንግሥት በተለይ በጣም የሚጠቀምበት ነው፡፡ ቀበሌ ላይ ምዝበራ ፈጽሟል ተብሎ አቤቱታ የቀረበበት ሰው ለበለጠ ማዕረግ ታጭቶ የወረዳ አስተዳዳሪ አድርገው ከቀበሌው ያስወግዱታል፡፡ ወረዳ ላይም እንዲህ ያደረገውን ለዞን፤ዞን ላይ ያደረገውን ክልል ላይ፤ ክልል ላይም እንዲህ ያደረገውን ፌዴራል ላይ መሾም የተለመደ አሠራር ነው፡፡ አሁን አሁን በቤተክርስቲያናችንም ያሉ መሪዎች ይህንን አሠራር የያዙት ይመስላል፡፡ በዲቁና ያልታመነውን ለቅስና ያበቁታል፡፡ ለቅስና ያልበቃውን ሰው ለቁምስና ይሾሙታል፡፡ ለቁምስናም ብቁ ያልሆነን ሰው ለጵጵስና ያጩታል፡፡ ይህ አሠራር ለቤተ ክርስቲያናችን ከባድ አደጋ ነው ስለዚህ ሁላችንም ልንታገለው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ እስኪ እነዚህን ለቤተክርስቲያናችን ለጵጵስና ማዕረግ ይበቃሉ ተብለው እጩ ሆነው የቀረቡትን ስም ዝርዝር ተመልክታችሁ ለሚመለከተው አካል እውነተኛውን መረጃ እንድታደርሱ ይሁን፡፡ ይህ ጉዳይ ለሁላችን ነውና፡፡ እዚህ ላይ ግን ይህን የጻፍኩት ዛሬ እውነተኛ እና ለሁሉ መካሪ አስተማሪ የሚሆን ለጵጵስና የሚበቃ የለም ለማለት ፈልጌ አይደለም፡፡ አሉ እዚህ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት መካከል ሊቃውንት አሉ፡፡ ግን የታወቁ አሉ ዓላማቸው ጵጵስናውን ተንተርሰው ቤተክርስቲያናችንን ለመናፍቃን አሳልፈው ለመስጠት ፈርመው የመጡ፡፡ ስለዚህ እነዚህን እጩዎች ተመልክተን ሁላችን አጥርተን እውነተኛውን መረጃ ለሚመለከተው አካል እንድናሳውቅ የበኩላችንን የቤተክርስቲያን ልጅነታችንንም እንድናስመሰክር ይህንን ጻፍኩት፡፡ የዕጩዎቹን ዝርዝር ከ “ሐራ ዘ ተዋሕዶ” ወስጀዋለሁ፡፡ አነሆ!!!
እስከ አኹን ድረስ በተለያዩ መንገዶች የተጠቆሙና በአብዛኛውም አስመራጭ ኮሚቴው ከብፁዓን አባቶች እንደተቀበላቸው የተገለጹ ቆሞሳትና መነኰሳት ስም ዝርዝር፤
1.  አባ ዘውዱ በየነ/የደብረ ብርሃን ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
2.  አባ ኃይለ ማርያም አረጋ/የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ/
3.  አባ ያሬድ ምስጋናው/የእንጦጦ ኪዳነ ምሕረት መጻሕፍትና ድጓ መምህር/
4.  አባ ገብረ ሥላሴ ጠባይ/የጎፋ ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል አስተዳዳሪ/
5.  አባ ዘርዓ ዳዊት ኃይለ ሥላሴ/የመርካቶ ቅዱስ ራጉኤል አስተዳዳሪ/
6.  አባ ፍቅረ ማርያም ተስፋ ማርያም/የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም አስተዳዳሪ/
7.  አባ ኃይለ ጊዮርጊስ/ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
8.  አባ ገብረ ጻድቅ ደበብ
9.  አባ ሣህለ ማርያም ገብረ አብ/አሜሪካ ‐ ቨርጂንያ)
10.         አባ ኃይለ ሚካኤል ወልደ ሐዋርያት/የደብረ ሊባኖስ ገዳም መጽሐፍ መምህር/
11.         ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለ ሃይማኖት/የናዝሬት ቅድስት ማርያም አስተዳዳሪ/
12.         አባ ኃይለ ሥላሴ ገብረ እግዚአብሔር/አሜሪካ ‐ ሎስ አንጀለስ/*
13.         አባ ፊልጶስ ከበደ /አሜሪካ ‐ቨርጂንያ/
14.         አባ ጽጌ ገነት ወልደ ኪዳን/አሜሪካ ‐ቨርጂንያ/
15.         ጸባቴ አባ የማነ ብርሃን(አዳሙ) ዓሥራት/አሜሪካ ‐ ቨርጂንያ/
16.         አባ ለይኩን ግፋ ወሰን/ደብረ ሊባኖስ ገዳም/
17.         አባ ፍቅረ ማርያም/ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም አስተዳዳሪ/
18.         ዬኔታ ጳውሎስ/ደብረ ሊባኖስ ገዳም/
19.         አባ ልሳነ ወርቅ ደለለኝ/ደብረ ጽጌ ገዳም/
20.         አባ መሐሪ ሀብቴ/አኵስም/
21.         አባ መርሐ ጥበብ ተሾመ/የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ገበዝ/
22.         አባ ኢሳይያስ/የዝቋላ ገዳም አበምኔት/
23.         አባ ማቴዎስ ከፍያለው/እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት/
24.         አባ ገብረ ሕይወት ፍሥሓ/ጀርመን ‐ ሙኒክ/
25.         አባ ገብረ ሐና ታደሰ/ዱባይ/
26.         አባ ገብረ መድኅን ወልደ ሳሙኤል(ኳታር)*
27.         ዶ/ር አባ ኃይለ ማርያም መለሰ/የጠቅላይ ጽ/ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ/
28.         አባ ኪዳነ ማርያም ደስታ/የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ቀሲስ/
29.         አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል/የጠቅላይ ጽ/ቤት የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ዋና ሓላፊ/
30.         አባ ሞገስ ኃይለ ማርያም/የመናገሻ ቅድስት ማርያም አስተዳዳሪ/
31.         አባ ዘድንግል ኑርበገን/ፈረንሳይ/
32.         አባ ገብረ ማርያም ገብረ ሥላሴ/መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የገዳማት መምሪያ ዋና ሓላፊ/
33.         አባ ገብረ ጻድቅ ዐረፈ ዓይኔ/የአኵስም ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
34.         አባ መንግሥተ ኣብ ገብረ ሥላሴ/የቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል አስተዳዳሪ/
35.         አባ ገብረ አድኃኔ ወልደ ማርያም/የደብረ መንከል ገዳም አስተዳዳሪ/
36.         አባ ጥዑመ ልሳን/ማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም አስተዳዳሪ/
37.         አባ ወልደ መድኅን ተክለ ብርሃን/እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት/
38.         አባ ዘተክለ ሃይማኖት/የደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ካቴድራል ሰባኬ ወንጌል/
39.         አባ ወልደ ገብርኤል አማረ/ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የትርጓሜ መምህር/
40.         አባ ኢሳይያስ/ድሬዳዋ ቅድስት ሥላሴ
41.         ንቡረ እድ አባ ገብረ ሕይወት/ድሬዳዋ ቅዱስ ገብርኤል አስተዳዳሪ/
42.         ሊቀ ሊቃውንት አባ ዕዝራ ሐዲስ/ጎንደር መጻሕፍት መምህር/
43.         ሊቀ ጉባኤ አባ ገብረ ማርያም ገብረ መስቀል/ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም/
44.         አባ ኪዳነ ማርያም ሞላልኝ/ባሕር ዳር/
45.         አባ ብርሃነ መስቀል ደርበው/አዘዞ/
46.         አባ ቴዎድሮስ መስፍን/የሊቃውንት ጉባኤ አባል/
47.         አባ ወልደ ጊዮርጊስ ጸጋው/ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም መምህር/
48.         አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎሬዎስ/ጎፋ ጥበብ እድ ሥራ አስኪያጅ/
49.         አባ ኃይለ ማርያም/ሐዋሳ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
50.         አባ ተክለ ማርያም አምኜ/አስኮ ቅዱስ ገብርኤል አስተዳዳሪ/
51.         አባ ገብረ ሥላሴ ጎበና/ካርቱም ሀገረ ስብከት/
52.         አባ ብርሃነ መስቀል ተድላ/ጀርመን ‐ በርሊን/
53.         አባ ኄኖክ ተክለ ጊዮርጊስ/መካኒሳ ቅዱስ ሚካኤል አለቃ/
54.         አባ ብንያም ከበደ/የሆሳዕና ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
55.         አባ ገብርኤል ወልደ ዮሐንስ
56.         አባ ሰይፈ ገብርኤል ኦብሰን/አሜሪካ ‐ ሲያትል/*
57.         አባ ሚካኤል ገብረ ማርያም/የዱራሜ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
58.         አባ ስብሐት ለአብ/ጀርመን/
59.         አባ ኢያሱ ገብረ አልፋ/የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ቅኔና መጻሕፍት መምህር/
60.         አባ ኃይለ ሚካኤል/መቐለ ቅዱስ ጊዮርጊስ አስተዳዳሪ/
61.         አባ ኃይለ ሚካኤል ወልደ ሚካኤል/የደብረ ሊባኖስ ገዳም መምህር/
62.         አባ ፍቅረ ዮሐንስ ገብረ ሕይወት/ሐይቅ እስጢፋኖስ አበምኔት/
63.         አባ ኤልያስ ታደሰ/የደሴ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ/
64.         መልአከ ሰላም አባ ገብረ ኪዳን/አሜሪካ ‐ ቬጋስ/
65.         አባ ተክለ ሃይማኖት/ዋሽግንተን ዲሲ/
66.         አባ ፍቅረ ማርያም/ዋሽንግተን ዲሲ/
67.         አባ ገሪማ አያልቅበት/ዱባይ/
68.         አባ ብርሃነ መስቀል ዕንቁ
69.         አባ ወልደ ትንሣኤ አባተ/የቅዱስ ላሊበላ ደብር አስተዳዳሪ/
70.         አባ ጌዴዎን/አሜሪካ ‐ ፍሎሪዳ/
71.         አባ ገብረ ኪዳን እጅጉ/
72.         አባ ቀለመ ወርቅ/ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም/
73.         አባ ወልደ ሐና ጸጋው/የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ/
74.         ሊቀ ጉባኤ አባ ሳሙኤል/ኢጣልያ/
75.         አባ ገብረ ማርያም/ዱባይ/
76.         አባ ገብረ ሥላሴ/ኢየሩሳሌም ገዳም/
77.         አባ ኃይለ ኢየሱስ ተመስገን/የሽሮ ሜዳ ቅድስት ሥላሴ አስተዳዳሪ/
78.         አባ ዮሐንስ ገብረ ሥላሴ/የወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
79.         አባ ሀብተ ማርያም ገብረ መስቀል/ሲዳማ ጌዴኦ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
80.         አባ ተክለ ማርያም ስሜ/ሐዋሳ/
81.         አባ ኃይለ መለኰት ተስፋ ማርያም/ጀርመን/
82.         አባ ኃይለ ሚካኤል/ኢየሩሳሌም ገዳም/
83.         አባ ኃይለ ጊዮርጊስ/ሲውዘርላንድ/
84.         አባ ላእከ ማርያም ገብረ ጊዮርጊስ/ዓዲ ግራት/
85.         አባ ገብረ ኪዳን/ማይጨው/
86.         አባ ዮሐንስ ከበደ/አየር ላንድ/
87.         አባ ገብረ ኢየሱስ መኰንን /እንጦጦ ቅድስት ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ/
88.         አባ ገብረ መድኅን/ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም መምህር/
89.         አባ ሳሙኤል ገላነው/የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ኮሌጅ መምህር/*
90.         አባ ፈቃደ ሥላሴ/ዋሽንግተን ዲሲ/
91.         አባ ወልደ ማርያም አድማሱ/የደብረ ገዳም ጸባቴ/
92.         አባ ገብረ ሥላሴ በላይ/የደሴ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
93.         አባ ጽጌ ሥላሴ መዝገቡ/የደሴ ቅዱስ ገብርኤል አስተዳዳሪ/
94.         አባ ናትናኤል/የአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት አስተዳዳሪ/
95.         አባ ቃለ ጽድቅ ሙሉጌታ/የጠቅላይ ጽ/ቤት ውጭ ጉዳይ መምሪያ ሓላፊ/
96.         አባ መልአኩ/ቅዱስ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ኮሌጅ/
97.         አባ ተክለ ሃይማኖት ንጉሤ/የጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ/
98.         አባ ወልደ ዐማኑኤል/አሜሪካ/
99.         አባ ገብረ ጻድቅ/ምዕራብ ሸዋ/
100.       አባ ክንፈ ሚካኤል ልሳኑ/መንበረ ፓትርያርክ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር/
101.       አባ ገብረ ማርያም/ደቡብ አፍሪካ/
102.       ዬኔታ ይባቤ በላይ/ምዕራብ ጎጃም የሐዲሳትና የቅኔ መምህር/
103.       ሊቀ ሥልጣናት አባ ገብረ ሥላሴ/መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል/
104.       አባ ዘርዓ ዳዊት/አሜሪካ ‐ ሚኒሶታ/
105.       አባ ወልደ ሰማያት/አሜሪካ ‐ ሲያትል/
106.       አባ እስጢፋኖስ/ዋሽንግተን ዲሲ/
107.       አባ ዘሚካኤል ደሬሳ/ዴንማርክ/
108.       አባ ዕንቁ ሥላሴ ተረፈ/መዝገበ ምሕረት ካራ ቆሬ ፋኑኤል አስተዳዳሪ/

የመመልመያው መሥፈርት የሚከተለው ነው፡፡
1.  በሥርዓተ ምንኵስና በታወቀ ገዳም በድንግልና መንኵሶ በክህነት ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግልና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ዕጩ ኾኖ የተመረጠ፤
2.  ከመነኰሰበት ገዳም ስለ ምንኵስና ሕይወቱና ስለ ክህነቱ በቂ ማስረጃ ማቅረብ የሚችልና በመነኰሰበት ገዳም በቅንነትና በታማኝነት ቢያንስ ለአምስት ዓመት ያገለገለ መኾኑ የተረጋገጠለት፤
3.  ለሀገር ውስጥ አገልግሎት ወይም ኢትዮጵያውያን ለሚኖሩበት የውጭ ሀገረ ስብከት የሚሾም ከኾነ ዜግነቱና ትውልዱ ኢትዮጵያዊ የኾነ፤
4.  በውጭ ሀገር ለሚገኙና የውጭ ሀገር ዜጎች ከራሳቸው መካከል አባት መሾም እንዲቻል በቅድሚያ ከመካከላቸው ወደ አገር ቤት መጥተው አስፈላጊውን ትምህርት እንዲያገኙ፤ ሥርዓተ ገዳምና ሥርዓተ ምንኵስናን እንዲያውቁ ይደረጋል፤
5.  ኢትዮጵያውያን ያልኾኑ ወይም ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሚኖሩበት የውጭ ሀገረ ስብከት የሚሾም ከኾነ፤ ዜግነቱ/ትውልዱ ኢትዮጵያዊ የኾነ ወይም ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ወገን የኾነ ወይም ኢትዮጵያዊ ኾኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት ተቀብሎ በሥርዓተ ክህነት መቀደስና ማስተማር የሚችል፤ እስከ ቆሞስነት ደረጃ የደረሰ በሚሾምበት ሥፍራ ለማገልገል የትምህርት ዝግጅትና የቋንቋ ችሎታና ብቃት ያለው፤
6.  የብሔረሰቡ ተወላጅ የኾነና በብሔረሰቡ ቋንቋ የማስተማር ችሎታ ያለው ወይም ተወላጅነቱ ሌላ ብሔረሰብ ኾኖ በተሠየመበት ሀገረ ስብከት በብሔረሰቡ ቋንቋ ማስተማር የሚችል፤ እንዲኹም በብሔረሰቡ ቋንቋ የሚናገር ከሌለ ቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ሕይወቱ የታመነበት አባት ይመድባል፡፡
7.  ለአንድ ቦታ አምስት ተጠቋሚዎች ለግምገማ የሚቀርቡ ሲኾን፤ ለምርጫ ቀርበው የሚወዳደሩት ግን ኹለት ናቸው፤
8.  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት/ነገረ መለኰት/ በቂ ዕውቀትና የማስተማር ችሎታ ያለው፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓተ ቀኖና ጠንቅቆ ያወቀ ለመኾኑ የተረጋገጠ ማስረጃ ያለው፤ ከቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤቶች ቢያንስ በአንድ ጉባኤ የተመረቀ፣ ወንበር ዘርግቶ ያስተማረ ቢኾን፤ ቢቻል ኹለገብ የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ዘመናዊ ትምህርት ያለው ኾኖ ከመንፈሳዊው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቢያንስ ዲፕሎማ ያለው፤
9.  በመንፈሳዊ ሕይወቱና በግብረ ገብነቱ በአስተዳደር የሥራ ልምዱና በሥራ አመራር ችሎታና ብቃቱ በነበረበት አካባቢ/የሥራ ቦታ/ በሚገኙ ሊቀ ጳጳስ ሰብሳቢነት በካህናትና በምእመናን የተመሰከረለት ስለመኾኑ የተረጋገጠለት፤
10.         የምእመናንንና የካህናትን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ችግር የመረዳትና የችግር አፈታት ልምድና ችሎታ ያለው፤
11.         የቤተ ክርስቲያኒቱ ቋንቋ የኾነውን ግእዝ በሚገባ የሚያውቅ ኾኖ ቢቻል ከዓለም አቀፍ ቋንቋዎች አንዱን የሚያውቅ፤
12.         በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ጽኑዕ የኾነ፤
13.         ሙሉ አካል ያለውና ጤንነቱ የተሟላ፤
14.         ዕድሜው ከ45 እስከ 60 ዓመት የኾነ፤
15.         ቢቻል የተሾመበትን ሀገረ ስብከት ቋንቋ የሚያውቅ፤
16.         አዲስ አበባ ሀገረ ስብከትም እንደ ሌሎች አህጉረ ስብከት ጥቆማ የመስጠት ድርሻው የተጠበቀ ነው፤

17.         በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ለኤጲስ ቆጶስነት እንዲሾሙ የተመረጡት ቆሞሳት፣ ከመሾማቸው በፊት ስለ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንና የሥራ አመራር በአባቶች፣ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በምሁራን የሦስት ወራት ሥልጠና እንዲሰጣቸው ይደረጋል፡፡

No comments:

Post a Comment