© በመልካሙ በየነ
ታህሳስ 14/2008 ዓ.ም
ደብረማርቆስ፣
ኢትዮጵያ

ሌላው የሚገርመው ነገር የጴጥሮስ መልስ ነው፡፡
ጴጥሮስ እንዲህ አለ “ሁሉም ባንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም” እንግዲህ ጴጥሮስ በራሱ ተመክቶ ነገ የሚሆነውን የሚደረገውን
ነገር ስላላወቀ ከሁሉም ይልቅ ጌታውን አብልጦ እንደሚወደውና ከእርሱም እንደማይሸሽ ፈጥኖ ተናገረ፡፡ ኢየሱስም እንዲህ አለው “እውነት
እልሃለሁ በዚች ሌሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” ጴጥሮስ ግን አሁንም በራሱ እንደተመካ ነበር “ከአንተ ጋራ መሞት እንኳ
የሚስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም አለ” አምላኩ የሚነግረውን እንኳ ማመን አቃተው፡፡ እስከሞት ድረስም እንደሚታመን በራሱ አንደበት
ተናገረ፡፡ በእውነት ግን ጴጥሮስ በዚያች ሌሊት እስከሞት ድረስ ይታመን ይሆን? እናንተ ማቴ 26ን በሙሉ እያነበባችሁ ተከተሉኝ
አሁን ይሁዳ መምህር ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን ብሎ ስሞ ለአይሁድ አሳልፎ ሰጥቷቸዋል፡፡ እነርሱም ወደሊቀ ካህናቱ ቀያፋ ወሰዱት፡፡
በዚህ ጊዜ ያ ማንም ቢክድህ አልክድህም እስከሞት ድረስ እከተልሃለሁ ያለው ጴጥሮስ እስከዚህ ግቢ ድረስ በሩቅ ሆኖ ነበር የሚከተለው፡፡
የአይሁድ ጭፍሮችን ፈራ ነገር ግን ደግሞ አልክድህም ያለው ቃል አሰረው ስለዚህ በሩቅ ሆኖ መከተሉን መረጠ፡፡ ቁጥር 69 ላይ ቅዱስ
ጴጥሮስ ከቤቱ ውጭ በዐጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር አንዲት ገረድም ቀርባ አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው፡፡ እርሱ
ግን የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ፡፡ በተድላና ደስታ ዘመን ምንም መከራ ሳይኖር እስከሞት ድረስ እታመናለሁ ብሎ በአፍ
መናገር እስከሞት ድረስ መታመን ማለት አይደለም፡፡ አሁንም ደግሞ ሌላኛዪቱ እንዲህ ጠየቀቸው አሁንም አላውቀውም ብሎ ካደ፡፡ አሁንም
ለሦስተኛ ጊዜ አነጋገርህ ይገልጥብሃልና በእውነት አንተ ከእርሱ ወገን ነህ አሉት ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ለሦስተኛ ጊዜ ካደ፡፡
ከዚህ በኋላ ዶሮ ጮኸ የዚያን ጊዜ ያ ኢየሱስ ክርቶስ የነገረው ቃል ትዝ አለውና መራራ ልቅሶን አለቀሰ፡፡ አሁን በዚህ በመከራው
ሰዓት የ5 ገበያ ሕዝብ የለም ቢኖር እንኳ ለመስቀል እንጅ እንዳይሰቀል ለመከልከል አይደለም፡፡ ሌሎችም ደቀመዛሙርት እንዲሁ በየፊናቸው
ልብሳቸውን ጥለው ሁሉ የሸሹ አሉ፡፡ (ማር 14÷51-52) ታዲያ እስከመጨረሻ የጸናው ማነው?
ይቀጥላል…
No comments:
Post a Comment