© መልካሙ በየነ
መጋቢት 23/
2009 ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ፣ ኢትዮጵያ

ለሰማያዊ ልደቱ እናት እንደሌለችው ሁሉ ለምድራዊ ልደቱም አባት የሌለው እንደሆነ ሊቃውንቱ እንዲህ ያስተምራሉ፡፡
እዚህ ላይ ለቀዳማዊ ልደቱ መለኮታዊት እናትም ሆነች ሥጋዊት እናት የለችውም ማለት ነው፡፡ ለምድራዊ ልደቱም እንደዚሁ መለኮታዊም
ሆነ ሥጋዊ አባት የለውም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት የአብ አባትነት ቀድሞ ዘመን ሳይቆጠር የነበረ አሁንም ያለ ወደፊትም የሚኖር ነው ማለት ነው፡፡ አባትነት እንደ ቀበሌ መታወቂያ
በየዘመኑ የሚታደስ አይደለም፡፡ ስለዚህ ለምድራዊ ልደቱ አብ በድጋሜ አባቱ ሆነ ዳግም በማኅጸነ ማርያም ወለደው አይባልም ቢባልም
ክህደት እና ጥፋት ነው፡፡ ይህንንም የምንለው በማስረጃ አስደግፈን ነውና ማስረጃውን እናስቀምጣለን፡፡

2.
ሃይማኖተ አበው
ዘጎርጎርዮስ ም 35 ቁ 17 “በምድራዊ ልደቱ አባት አለው አትበሉ በሰማያዊ ልደቱም እናት አለችው አትበሉ እርሱ በምድር አባት
የሌለው ነው በሰማይም እናት የሌለችው ነው”
3.
“ዘአልቦቱ
እም በሰማያት ወአብ በዲበ ምድር ፤ በሰማይ እናት በምድርም አባት የለውም” አንቀጸ ብርሃን ዘቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ፡፡
4.
ሃይማኖተ አበው
ዘሄሬኔዎስ ም 7 ክ 2 ቁ 20 “ከንጽሕት ድንግል ማርያም በኋላ ዘመን እንደተወለደ እንደሚነግሩን ቀድሞም ከአብ እንደተወለደ እንዲሁ
ከአባት ያለእናት ከእናት ያለአባት ለመወለድ መጀመሪያ እርሱ እንደሆነ ለፍጥረት ሁሉ ይነግሩናል”

6.
ሃይማኖተ አበው
ዘኤጲፋንዮስ ም 54 ቁ 11 “አብ ጥንት ፍጻሜ የሌለው ቃልን ዓለምን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ወለደው በኋላ ዘመንም በግብረ መንፈስ
ቅዱስ ንጽሕት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ”… ይህንን አጻጻፍ ልበ ብላችሁ አስተውሉት፡፡ አብ
በማኅጸን ወልዶት ቢሆን ኖሮ “በኋላ ዘመንም በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ወለደው” ለማለት
የቀና የተመቸ አጻጻፍ ነበር ነገር ግን አብ በማኅጸነ ማርያም ከአብ አልተወለደምና “ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ” ብሎ
ሊቁ ኤጲፋንዮስ ከላይ ባለው መልኩ ጻፈልን፡፡
7.
ሃይማኖተ አበው
ዘሳዊሮስ ም 84 ቁ 8 “ሁለት ልደት እንዳለው በእግዚአብሔር ቃል እንዲሁ ልናምን ይገባናል አንዱ ቅድመዓለም ከአብ ያለ እናት
የተወለደው የማይመረመር ልደት ነው፡፡ ሁለተኛውም በኋላ ዘመን ከንጽሕት ድንግል ማርያም ያለአባት የተወለደው የማይመረመር የማይነገር
ልደት ነው፡፡ ነገር ግን ቃል ሥጋ እንደሆነ ባሕርያችንንም ባሕርይ እንደአደረገ በዓይናችን እንዳየነው በእጃችንም እንደዳሰስነው
ይህን ብቻ እናውቃለን”
እነዚህ ሰባት ማስረጃዎች በዋናነት ሁለት መሠረታዊ ነጥብ የያዙ ናቸው፡፡
1.
ለሰማያዊ ልደቱ
እናት ለምድራዊ ልደቱ ደግሞ አባት እንደሌለው የሚገልጹ መሆናቸው፡፡
2.
የጌታ ልደታት
ሁለት መሆናቸውን እነርሱም ቅድመዓለም ከአብ በመለኮት ድኅረ ዓለም ከእመቤታችን በሥጋ የተወለዳቸው ልደታት ብቻ መሆናቸውን፡፡ እዚህ
ላይ “አብ በማኅጸነ ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ወለደው” የሚለው የቅብዓቶች ሦስተኛ ልደት ደጋፊ የሌለው ከንቱ ፍልስፍና መሆኑን
ተረድተንበታል፡፡
በቀጠዩ ክፍል የጌታ ሁለቱን ልደታት ሊቃውንት መምህራን በሃይማኖተ አበው ያሠፈሩትን ከእነዚህ ሰባት ማስረጃዎች
በተጨማሪ ሌሎች ዐሥራ ዐራት ማስረጃዎችን እንጽፋለን፡፡ በነገራችን ላይ እነዚህ ማስረጃዎች ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ እኔ በጥቂቱ
ነው የምጽፋቸው ተጨማሪውን ለማንበብ መጽሐፉን እንድትመለከቱ ከወዲሁ አሳስባለሁ፡፡
ይቆየን፡፡
ይቀጥላል፡፡
No comments:
Post a Comment