
ዛሬ
ዛሬ ከዚህ ሰው በከፋ ችግር ውስጥ ያለን በርካታ ሰዎች አለን፡፡ ከግለሰብ እስከ ቡድን፣ ከነጠላ እስከ ማኅበራት፣ከተማሪ እሰከ አስተማሪ፣ ከቀበሌ እስከ ፌዴራል፣ ከክልል እስከ አገር ድረስ ሳናውቅ በምንከራያቸው
ነገሮች በጣም ስቃይ ጸንቶብናል፡፡ አንድ ሰው ባለማዎቅ ከልብሱ ጋር በሚገዛው ጽሑፍ ይሸማቀቃል፡፡ አንዲት እርጉዝ ሴት “I
AM VIRGIN” የሚል ልብስ ለብሳ ስትሄድ ሰው ቢስቅባት ሳቁን ከማስተናገድ ውጭ የለበሰችው ልብስ ላይ የተጻፈውን ነገር አትረዳውም፡፡
አንዱ ደግሞ ያገኘው ሰው ሁሉ ባገኘው ነገር ይመታዋል፡፡ ለምን እንደሚመቱት ግን አያውቅም፡፡ ለካስ “KICK ME” የሚል ጽሑፍ
ከልብሱ ላይ ተጽፏል፡፡ ሳናውቅ በምንሰራቸው ሥራ፤ ሳንረዳ በምንገለብጠው ነገር ሁሉ ተጠቂዎች ራሳችን ነን፡፡ ቆዩ እንጅ ግን የማናውቀውን
የምንሠራ እና የምንገለብጥ እኛ ኢትዮጵያውያን ብቻ ነን እንዴ? ሰው የማያውቀውን እያደረገ በመከራ ይኖራል፤ መንግሥት የማያውቀውን
ሕግ እየገለበጠ አገዛዝ ያከፋብናል፡፡ ተማሪው መልስ መሆን አለመሆኑን ሳይረዳ ከጓደኛው ይኮርጃል (ይሰርቃል)፤ አረ አንዳንዱስ
ከነ ስሙም የሚኮርጅ አለ አሉ፡፡ የማናውቀውን ስንሠራ ትንሽ ኃፍረት የማይሰማን ግን ለምንድን ነው? አገርን ያህል ነገር በተቀዳ
ፖሊሲ፣ በተኮረጀ እቅድ፣ ይጥቀም አይጥቀም በማይታወቅ አስተሳሰብ ስናስተዳድር ትንሽ አይሰቀጥጠንም፡፡ አይጥና ዝንጀሮ ለላብራቶሪ
ምርመራ እንደሚጠቀሙባቸው ሁሉ እኛን ኢትዮጵያውያንንም የፖሊሲ፣ የስታራቴጅ፣ የአመለካከት፣ የአስተሳሰብ መፈተኛ ቤተሙከራዎች ያደረጉን
በርካቶች ናቸው፡፡ ለማንኛውም ቢያንስ በራሳችን መፍታት የምንችላቸውን ቀላል ነገሮች መፍታት የተሻለ ስለሆነ ሥራን ከመስራታችን
በፊት ጥቅሙን፣ ለምን እንደምንሰራው፣ መቼ እንደምንሠራው፣ እንዴት እንደምንሠራው ማወቅ ያስፈልጋል፡፡
des yilal
ReplyDeletedes yilal
ReplyDelete