© መልካሙ በየነ
ግንቦት 29/2009
ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ፣ ኢትዮጵያ
ተጽሕፈ እም አሐዱ ሊቅ ኢትዮጵያዊ
ኅሩይ ወመፈክራዊ
ጌታው አለቃ ኅሩይ
፲፭ኛ አንቀጽ
ምዕዳንና አኲቴት

መፍትሔ ቃላት
ሁከት - ሁልጊዜ የሚከናወን
የባሕር እንቅስቃሴ፡፡
ሃይማኖተ አበው - የመጽሐፍ
ስም፣ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ፣ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ የቀድሞ ሊቃውንት ያስተማሩትን ትምህርት የያዘ የቤተ ክርሰቲያን መጽሐፍ፡፡
ሕልው- ነዋሪ፣ ቋሚ፡፡
ለባዊያ- የሚያስቡ፡፡
ሕላዌ -አኗኗር፡፡
ሕያዋን - በማይለወጥ ሕይወት
የሚኖሩ ሕይወት ያላቸው፡፡
መለኮት- የእግዚአብሔር የአንድነት
መገለጫ እና የግዛትና የጌትነት መጠሪያ ስሙ፡፡
መልክእ -መልክ፡፡
መቅድመ ወንጌል- የመጽሐፍ
ስም፣ የአራቱ ወንጌላት መቅድም፣ አሞንዮስ፣ አውሳብዮስ በሚባሉ ሊቃውንት እንደተጻፈ የሚነገርለት ስለ ጥንተ ተፈጥሮ ስለ ሰው ጠባይና
በተፈጥሮው ስለተሰጠው ነጻነት በሰፊው የሚናገር፡፡
መንፈስ ቅዱስ- ከሦስቱ አካላት
የሦስተኛው አካል የመንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም፡፡
ማሕደር- ማደሪያ፣ ቤት፡፡
ምሥጢረ ሥላሴ- ስለ እግዚአብሔር
አንድነት ሦስትነት ቤተ ክርስቲያን የምታስተምረው ትምህርት፡፡
ምዕዳን - ምክር፡፡
ሥላሴ- አብ ወልድ መንፈስ
ቅዱስ፡፡
ሥልጣን- የበላይነት፣ አገዛዝ፡፡
ርጥበት - ውኃ ያለበት የባሕር
አካል፡፡
ስመ አካል- የአካል ስም፡፡
ስመ ኩነት- የመሆን፣ የአኳኋን
ስም፡፡
ስመ ግብር- የግብር ስም፡፡
ሰራጺ- የመንፈስ ቅዱስ የግብር
ስም፣ ከአብ የወጣ የተገኘ፡፡
ሰብእ- ሰው፡፡
ስፍሀት- ስፋት፡፡
ቅሉ-ቢሆን፣ ጨምሮ፣ ከዚያም
በላይ፣ ለነገሩ፡፡
ቅጥነተ ሕሊና- የረቀቀ አስተሳሰብ፣
ረቂቅ አእምሮ፣ ጥልቅ አስተሳሰብ፣ ምርምር፣ ርቃቄ፡፡
ባሕርይ- ትርጉሙ ብዙ ነው
እንደ ሁኔታው ይለያያል፣ በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት እግዚአብሔር በባሕርይው አንድ ነው፡፡
ተረክቦ- መገኘት፡፡
ተወላዲ- የወልድ የግብር
ስም፣ ከአብ የተወለደ፡፡
ተድኅሮ -ወደ ኋላ መቅረት፡፡
ተፈልጦ- መለየት፡፡
ትርጉም- በግዕዝ የተጠቀሰው
ንባብ ፍች (በአማርኛ) ማለት ነው፡፡
ትስብዕት- ሰው መሆን፣ የሰውነት
ባሕርይ፣ ሰውነት፡፡
ትንሣኤ ዘጉባኤ- ጌታችን
ሁለተኛ ሲመጣ ሁሉም ሰው ተነሥቶ በአንድነት በፊቱ የሚቆምበት የትንሣኤ ጊዜ፡፡
ኃይለ ዘርዕ- እንደ ሰው
አራቱን ባሕርያት ነሥቶ ተወልዶ በየደረጃው ማደግ፡፡
ኃይለ እንስሳ- እንደ ሰው
መብላት፣ መጠጣት፣ መተኛት፣ መነሣት፡፡
ኃይለ ንባብ- እንደ ሰው
ደረጃ በደረጃ አፍ እየፈቱ አከናውኖ የመናገር ችሎታ፡፡
ኃይል- ብርታት፣ ኃይል፡፡
ኃዳሪ-አዳሪ፣ ኗሪ፣ በውስጥ
የሚኖር፡፡
ነባብያን- የሚናገሩ፡፡
ንባብ- ነገር፣ የመናገር
ችሎታ፡፡
ንባብ -በግዕዝ፣ ቃል በቃል
ከአንድ መጽሐፍ የተወሰደ ጥቅስ ማለት ነው በዚህ መጽሐፍ፡፡
አሐቲ ጠባይዕ- የሕይወትነት
ጠባይ፡፡
አማልእክት- አምላኮች፡፡
አሠረ ፍኖት- ፈለግ፣ ፍለጋ፣
የመንገድ ፈለግ ወይም ኮቴ፡፡
አስማት- ስሞች፡፡
አስራጺ- የአብ የግብር ስም፣
መንፈስ ቅዱስን የሰረጸ ወይም ያስገኘ፡፡
አቃኒም- አካላት፡፡
አብ- ከሦስቱ አካለት የአንዱ
መጠሪያ ስም፤ በዚህ ስም ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ አይጠሩም፡፡
አእምሮ- ዕውቀት፣ ማስተዋል፡፡
አኮቴት- ምስጋና፡፡
አንቀጽ- መክፈያ፣ የመጽሐፍ
ክፍለ ሐሳብ ተጠናቆ ሌላ ሲጀመር እንደ ንዑስ ምዕራፍ ወይም ክፍል የሚያገለግል።
እዝነ ልቡና- የውስጥ የአእምሮ
ግንዛቤ፣ አእምሮ ላይ የተመሠረተ፣ በደንብ የሚሰማ ውሳጣዊ አካል፡፡
ከዊን - መሆን፡፡
ከዊነ ልብ- ልብ መሆን፣
የልብን ቦታ መያዝ፣ ወይም የአእምሮን የዕውቀትን ቦታ መተካት፣ ይህ ስም የአብ የከዊን ስሙ ነው።
ከዊነ ቃል- የወልድ የከዊን
ስሙ ነው፣ ቃል መሆን፣ በቃልነት መገለጥ ማለት ነው፣ ወልድ ለአብም፣ ለመንፈስ ቅዱስም፣ ለራሱም ቃል ነውና፡፡
ከዊነ እስትንፋስ - የመንፈስ
ቅዱስ የግብር ስሙ ነው፣ ለአብና ለወልድ እስትንፋስ፣ ሕይወት ሆኖ በራሱም ሕያው ነውና፡፡
ከርሠ መቃብር - የመቃብር
ሆድ፡፡
ክሂል- ችሎታ፡፡
ወላዲ- የአብ የግብር ስም፣
ወልድን የወለደ በመሆኑ “ወላዲ” ይባላል “ወላጅ” ማለት ነው፡፡
ወልድ- ከሦስቱ አካላት የሁለተኛው
አካል የወልድ መጠሪያ ስም፡፡
ዋሕድና- አንድነት፡፡
ዋዕይ- ሙቀት፡፡
ዕሪና- እኩልነት፣ መተካከል፡፡
ዝኒ ከማሁ- ይህም እንደዚያው
ነው፡፡ ምንጩ መገኛው ከላይ ከተጠቀሰው ጋር አንድ ነው ማለት ነው፡፡
ዮሐንስ ተአቃቢ- እግዚአብሔርን
በአካልም በመለኮትም ሦስት ብሎ ያስተምር የነበረ ዘጠኝ መለኮት ይላል የሚባል መናፍቅ ስም ነው። ትምህርቱ በደብረ ሊባኖስ ገዳም
እና በዋልድባ አካባቢ ተስፋፍቶ ነበር። አሁን ግን የጠፋ ይመስላል። ምንጩ ግን ትግራይ ነው ይባላል። ስሜን ሽዋ ነው የሚሉም አሉ።
ደብር- ተራራ፡፡
ገጽ- አካል፣ መልክ፡፡
ገጻት- አካላት፡፡
ፍኖት መብዕሰ- ያልተስተካከለ
ወጣ ገባ መንገድ፡፡
ተጽሕፈ እም አሐዱ ሊቅ ኢትዮጵያዊ
ኅሩይ ወመፈክራዊ
ጌታው አለቃ ኅሩይ
ተፈጸመ፡፡
No comments:
Post a Comment