፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አጫጭር መረጃዎች!

·
አቡነ ማርቆስን በመደገፍ አዲስ አበባ የሄዱ
ሥራ አስኪጆች ጸሐፊዎች እና ካህናት የውሎ አበላቸውን ከቤተክርስቲያኒቱ ሊወስዱ እንደሆነ ተነግሯል፡፡







ብጹእ አቡነ ዘካርያስ “ወልደ አብ” የተባለውን መጽሐፍ ለሊቃውንት ጉባዔ ካሳወቁ በኋላ “ሚሥጢረ ሃይማኖት
ወትንቢተ ዘዝክሪ ወጳውሊ” የተባለውን መጽሐፍ ገጽ በገጽ እየተመለከቱ እንደሆነ ታውቋል፡፡ ብጹእነታቸው ይህንን ሥራ እንደጨረሱ
ለሊቃውንት ጉባዔ አስቀርበው “ወልደ አብ” የሚገጥመውን ዕጣ ለዚህኛውም መጽሐፍ እንደሚያሰጡት ይጠበቃል፡፡
በምሥራቅ ጎጃም ጉዳይ
በጉባዔው ንቁ ተሳታፊ ሆነው እስከመሰደብ እና ስማቸው እስኪጠፋ ድረስ እየታገሉ ያሉት ብቸኛ አባት አቡነ ዘካርያስ እንደሆኑም ነው
የተነገረው፡፡ በነገራችን ላይ ብዙ የቅባት እምነት ተከታዮች አቡነ ዘካርያስን ለማሸማቀቅ እና ከዚህ ትግላቸው እንዲሸሹ ለማድረግ
ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን ይመሩ በነበሩበት ጊዜ ስለጠፋው ገንዘብ አብዝተው ይናገራሉ፡፡
ብጹነታቸው አቡነ ዘካርያስ ጠፋብኝ
ያሉትን ገንዘብ ያልካዱ ቃል በገቡት መሠረትም ከልጆቻቸውን ለምነው ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ያስረከቡ ናቸው፡፡
አንድ ነጥብ ስድስት
ሚሊዮን ብር ጠፋባቸው የተባሉት ብጹእነታቸው ያንን ብር አሁን ላሉት ሊቀ ጳጳስ በጉባዔ መካከል ማስረከባቸው ተዘግቧል፡፡ ነገር
ግን አሁን ያ ገንዘብ የት እንደገባ ምን እንደተሠራበት የተነገረ ነገር ስለሌለ በዚህ ጉዳይ መወቀስ የሚገባቸው አቡነ ዘካርያስ
ሳይሆኑ አቡነ ማርቆስ ናቸው፡፡ ብጹእ አቡነ ዘካርያስ የምሥራቅ ጎጃምን ህዝብ እንባ ለማበስ በንቃት እየታገሉ እንደሆነ መረጃው
ደርሶኛል፡፡ በፊት የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እያሉ አቡነ ዘካርያስ ከምሥራቅ ጎጃም እንዲነሡ በምእመናን አቤቱታ
ቀርቦባቸው እንደነበር የታወቀ ነው፡፡
ዛሬ ግን ያንን ለመካስ እየሠሩ ያሉ አባት ሆነዋል ተብሏል፡፡ ዛሬ የምንሰማው ሌላም ደስታ
እንደሚኖር ተስፋ አደርጋለሁ ለተዋሕዶ ልጆች ብቻ ማለቴ ነው፡፡
እዚህ ላይ አስተያየት ሊሰጡ የሚቋምጡ የቅባት እምነት ተከታዮች
አቡነ ዘካርያስን ምን ብለው እንደሚገልጿቸው ተመልከቱ፡፡ አቡነ ማርቆስስ የገዳመ አስቄጥስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ገዳም ገንዘቡን
ህጋዊ ሆነው ሊበሉት ይህንን ከታች አብሮ የተያያዘውን ደብዳቤ ሲጽፉ ምን አላችሁ ቃለ ዓዋዲው ስላዘዘ ነው ትሉ ይሆን በፍጹም!
አስተያየታችሁን ሚዛናዊ ለማድረግ ሞክሩ ያ ካልሆነ ግን #BLOCK ስላለ ዳግም አንተያይም፡፡
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍
© መልካሙ በየነ
ጥቅምት ፲፮
/ ፳፻፲ ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ፣
ኢትዮጵያ
✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍
No comments:
Post a Comment