Sunday, October 15, 2017

✍✝ቅዱስ ያሬድን በምን ቃል ነው የምንገልጸው?✝✍




፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ዛሬ ጽጌን ደጀን ደብረ አሚን ቤተክርስቲያን ነው ያሳለፍሁት፡፡ አምላክ ሲፈቅድ ሁሉ ይደረጋል፡፡ ምሽት አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ እዚህ ደብረ ማርቆስ ከሚገኘው ወንቃ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ልናድር ከአንድ ወንድሜ ጋር ወጣን፡፡ ነገር ግን ወደ መንገድ ስንወጣ ደጀን ሊወስደን የሚችል መኪና ነበር የፈለግን የገረመኝ እሱ ነው፡፡ ደግሞ መኪናው ተገኘ ከምሽት አንድ ሰዓት ተኩል በኋላ በአይሱዙ መኪና ተጭነን ደጀን ለሦስት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ደረስን፡፡ ከዚያም ወደ ደብረ አሚን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አመራን በዚያም አደርን፡፡ ደጀን ደብረ አሚን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ላይ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታቦት ተደርቦ ስለሚገኝ ሁሉንም ነገር አግኝተን ኪዳን አስደርሰን ወደ መነኸሪያ ሄድን፡፡
እኛ ስንሰማው ያደርነውን ጣዕሙ ልዩ የሆነውን ያሬዳዊ ዜማ በትንሹ ብናካፍላችሁስ ምናለበት ብለን አሰብንና ይኸው አዳምጡት ብለን ጋበዝናችሁ፡፡
‹‹እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፡፡
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፡፡
ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፡፡
ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፡፡
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ፡፡›› https://www.youtube.com/watch?v=Ez2JT9Lgfow
ሊቃውንቱን ስሟቸውማ እንዴት እንዴት አድርገው እንደሚያዜሙት፡፡ አቤት ያለው የልብ ደስታ ነፍስ ልትወጣ እኮ ነው የምትደርስ፡፡ ያሬድ ግን ምን ያለ ጸጋ ነው የተሰጠው ግን! ይህን የመሰለ ዜማ ከሰማይ ሰምቶ የመላእክትን ዝማሬ እኮ ነው ያስተማረን ያለማመደን፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=Wn9MS88yjHk
https://www.youtube.com/watch?v=DRteAbc572Q&t=131s

፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍
© መልካሙ በየነ
ጥቅምት ፭ / ፳፻፲ ዓ.ም
ደጀን፣ ኢትዮጵያ

✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍✝✍

No comments:

Post a Comment