.jpg)
ቁልፍ 1፡- ፲ቱ ትዕዛዛተ ኦሪት
ይህ የገነት ቁልፍ የሚከፈተው የሚከተሉትን አሥር መክፈቻዎች መያዝ ስንችል ብቻ ነው፡፡
፩. እግዚአብሔር አምላክህ እኔ
ነኝ፡፡ ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ፡፡
፪. የአምላክህን ሥም በከንቱ
አትጥራ፡፡
፫. የሰንበትን ቀን ትቀድሰው
ዘንድ አስብ፡፡
፬. አባትህንና እናትህን አክብር፡፡
፭. አትግደል፡፡
፮. አታመንዝር፡፡
፯. አትስረቅ፡፡
፰. በሐሰት አትመስክር፡፡
፱. ባልንጀራህን እንደ ራስህ
ውደድ፡፡
፲. የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፡፡
በእነዚህ አሥር መክፈቻዎች የመጀመሪያውን ቁልፍ ስንከፍት
ስድስት መክፈቻ ያለውን ሁለተኛ ቁልፍ ተቆልፎ እናገኛዋለን፡፡
ቁልፍ 2፡- ፮ቱ ሕግጋተ ወንጌል
ይህን
ቁልፍ ለመክፈት ስድስት መክፈቻዎችን መያዝ ይኖርብናል፡፡ እነዚህም፡-
፩. በወንድምህ ላይ በከንቱ አትቆጣ፡፡
፪. ወደ ሴት አትመልት በልብህም አታመዝር፡፡
፫. ሚስትህን ያለ ዝሙት ምክንያት በሌላ ነውር አትፍታ፡፡
፬. ፈጽመህ አትማል፡፡
፭. ክፉን በክፉ አትመልስ፡፡
፮. ጠላትህን ውደድ፡፡
ይህን ሁለተኛ ቁልፍ መክፈት ከቻልን
ጻድቃን የሚኖሩባትን ገነት መግባት የምችልበት ፈቃድ እናገኛለን፡፡ ነገር ግን ከእነዚህ አሥራ ስድስት መክፈቻዎች መካከል አንዲቷ እንኳ ብትጠፋን የገነት መግቢያ ፈቃድ ስለማናገኝ የጠፋብንን ቁልፍ በቀጥታ ወደ ካህናት በመሄድ ንስሓ
በመግባት መረከብ የምንችልበት መብት ስላለን ተረክበን ጉዟችንን መጠበቅ ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ቁልፎች ደግሞ በትክክል መክፈት እንዲችሉ ለማድረግ ተርቤ አብልታችሁኛል? ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል? እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛል? ታርዤ አልብሳችሁኛል? ታምሜ ጠይቃችሁኛል? ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋል? የሚሉትን ጥያቄዎች አሁን እየመለስናቸው መሆኑን ቆም ብለን ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ጉዞው ሩቅ ስለሆነ ለመመለስ የሚቻል ባለመሆኑ ከመጓዛችን በፊት የመክፈቻ ቁልፎችን መዘንጋት የለብንም፡፡ ካህናት አባቶቻችን
ያላቸው ሥልጣን ቀላል የሚመስለው ካለ ያ ሰው መክፈቻ በማያስፈልገው ሲኦል መቃጠሉ አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ገነት በዋዛና በፈዛዛ
ኖረን የምንገባባት ተራ ቦታ አይደለችምና፡፡ ማንም በኃጢአት የኖረ ሁሉ ያለምንም መክፈቻ ሲኦል ሊገባ ይችላል ገነትን ግን ያለ
መክፈቻ ከፍቶ የሚገባ ማንም የለም፡፡ ስለዚህ ገነት መግባት የምንፈልግ ሁሉ በቸርነቱ የሚሰጠንን መክፈቻ ከካህናት አባቶቻን ልንረከብ
ግድ ነው፡፡
No comments:
Post a Comment