Tuesday, February 26, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 20



====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው ።
ምዕራፍ ፩።
                  ******
፲፯፡ ወኵሎንኬ ትውልድ እምአብርሃሞ እስከ ዳዊት ፲ወ፬ቱ፡፡
                  ******
፲፯፡ ከአብርሃም እስከ ዳዊት አሥራ አራት ትውልድ ነው።
 ወእምዳዊት እስከ ፍልሰተ ባቢሎን ትውልድ ፲ወ፬ቱ።
ከዳዊት እስከ ፄዋዌ ፲፬ ትውልድ ነው። ወእምፍልሰተ ባቢሎን እስከ ክርስቶስ ትውልድ ፲ወ፬ቱ። ከፄዋዌ እስከ ክርስቶስ አሥራ አራት ትውልድ ነው።
ወኵሎንኬ ትውልድ እምአብርሃም እስከ ክርስቶስ ፵ ወ፪ቱ። ከአብርሃም እስከ ክርስቶ መላው አንድ ሁኖ ቢቈጠር አርባ ሁለት ነው። ፲ወ፬ቱ ፲፵፬ቱ ፲ወ፬ቱ ይላል። አርባ ሁለት ይሆናል። አሥራ አራት አሥራ ሰባት አሥራ ሁለት ይላል አርባ ሶስት ይሆናል። አሥራ አራት አሥራ ሰባት አሥራ አራት ይላል አርባ አምስት ይሆናል። አርባ ሁለት ያለ እንደ ሆነ ሁለቱን አግብቶ ሦስቱን ነገሥታት አውጥቶ። አርባ ሦስት ያለ እንደሆነ ከሦስቱ አንዱን አግብቶ ሁለቱን አውጥቶ። አርባ አራት ያለ እንደሆነ ከሁለቱ ከእመቤታችንና ከኤልያቄም አንዱን አግብቶ አንዱን አውጥቶ። አርባ አምስት ያለ እንደሆነ መላውን አግብቶ። ከፍ ብሎ አርባ ስድስት ዝቅ ብሎ አርባ አንድ ቢል ግድፈተ ጸሐፊ ነው። ተርትሮ የቈጠረውን ደምሮ፤ ደምሮ የቈጠረውን ተርትሮ ቈጠረ። ደምሮ የቈጠረውን ተርትሮ ተርትሮ የቈጠረውን ደምሮ ባይቈጥር አይሁድ ወንጌላዊ ተርትሮ መቊጠር እንጂ መደመር፤ መደመር እንጂ ተርትሮ መቊጠር አይሆንለትም ብለው ደገኛዩቱን ሕገ ወንጌልን ከመቀበል በተከለከሉ ነበርና።
አንድም ተርትሮ መቊጠር የሦስትነት ደምሮ መቊጠር ያንድነት ምሳሌ። አንድም ተርትሮ መቊጠር እንደ ሦስት ምስክር ደምሮ መቊጠር ቃሉ አንድ የመሆኑ ምሳሌ። ልማ በሥሉስ ጥፋ በሥሉስ እንዲሉ። አንድም በዳንኤል ልማድ ፸ ሰንበታተ አድሞሙ ለሕዝብከ ያለውን ተርትሮ የቈጠረውን ደምሮ፤ ደምሮ የቈጠረውን ተርትሮ እንደ ቈጠረ። አንድም በሦስቱ ክፍለ ዘመን የተቈጠረውን ባንድ በጌታ እንደተፈጸመ ለማጠየቅ። በዘመነ አበው በዘርዕከ ይትባረኩ ኵሎሙ አሕዛበ ምድር ተብሎ በዘመነ ነገሥት እስመ እምፍሬ ከርሥከ አነብር ዲበ መንበርከ በዘመነ ካህናት መቅደስ ትትሐነጽ እስከ ክርስቶስ ንጉሥ ወእምዝ ትትመዘበር ተብሎ የተነገረው ተስፋ ባንድ በጌታ እንደ ተፈጸመ  ለማጠየቅ።
አንድም ተርትሮ ቈጠረ ሥጋዊ ምግብና ሲለዋወጥ መጥቷል። በዘመነ አበው ምክር ተግሣፅ ሁኑዋል ያባት ለልጅ ያልፍ ነበር መጻሕፍት አልተጻፉም፤ በዘመነ መሳፍንት መጸሕፍት ተጽፈዋል መስቀል መቊረጥ ሁኑዋል። በዘመነ ካህናት እንደ ሁለቱም ሁኑዋል እንደ ዘመነ አበው ምክር ተግሣፅ ሁኑዋል። ያባት ለልጅ የማያልፍ ሁኑዋል። እንደ ዘመነ መሳፍንትም መስቀል መቊረጥ ሁኑዋል መጻሕፍት ተጽፈዋል። ደምሮ ቈጠረ መንፈሳዊ ምግብና ምንም በካህናት በኤጲስ ቆጶሳት እጅ ቢሆን አልተለወጠም አንድ ነው ለማለት።
አርባ ሁለት ባለው ለሰሎሞን ስድስት እርከን ያላት አትሮንስ ነበረችው።፡ እሱ በስድስተኛዪቱ ሁኖ ነገር ሲሰማ ሲፈርድ ይውል ነበር። ስድስቱ እርከን በሱባዔ ሲገቡት አርባ ሁለት ይሆናል። ያርባ ሁለቱ አበው ምግብና ሲፈጸም ጌታ ሰው የመሆኑ ምሳሌ። ሰሎሞን የጌታ አትሮንስ የእመቤታችን ምሳሌ።
አርባ ሶስት ባለው ለደብተራ ኦሪት አርባ ሦስት አዕማድ ነበሯት አርባ ሦስት አዕማደ ትስብእት አበው ሲፈጸሙ ጌታ ሰው ለመሆኑ ምሳሌ። አርባ አራት ባለው እስራኤል በአርባ አራተኛው ጉዞ ሰጢን ሰፍረው ርስታቸውን አይተው አድረዋል እንደዚህ ምዕመናንም ከአርባ አራተኛዪቱ ትውልድ ከእመቤታችን ተወልዶ ርስታቸው ጌታን አይተዋልና።
አርባ አምስት ባለው በአርባ አምስተኛው ጉዞ እየርስታቸው ገብተዋል። እንደዚህ ሁሉ ምዕመናንም አርባ አምስተኛ ትውልድ የሚሆን ርስታቸው ጌታን ይወርሳሉና።
                  ******
በእንተ ልደተ ክርስቶስ።
፲፰፤ ወለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመዝ ውእቱ ልደቱ።
፲፰፤ የነትዕማርን የነራኬብን የነሩትን ሲናገር መጥቶ ነበርና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደቱ እንዲህ ነው አለ።
                  ******
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
20/06/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment