Sunday, February 10, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 5


==================
ሦስተኛ ጉባኤ። 
ወአልበሶ አልባሰ ብሩሃ።
ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሮ ከእንስሳት ከአራዊት ለይቶ በነባቢት ነፍስ አከበረው ብሎ ነበርና ልጅነትን ሰጠው ፤ እስመ አልበሰክኒ ልብሰ ትፍሥሕት ወልብሰ መድኃኒት እንዲል።   
አካሉን ሲያይ ብሩህ አለ ፤ ሀብቱን ሲያይ አልባስ ብሎ አበዛ ፤ ከዚህ ዕለቱን አስመስሎታል አክሲማሮስ በ፵ ቀን ብሎ ለይቶ ተናግሯል።
ወገብረ ሎቱ ሥልጣነ ለርእሱ።
ሥራ ሠርቶ ሊጠቀምበት መንፈሳዊ  ዕውቀትን ሰጠው። 
ወአኅጥዖ ሞተ።
በዓቂበ ሕግ እንዳይሞት አደረገው።
ወረሰዮ ሥሉጠ ላእለ ኩሉ ፍጥረት ዘታሕተ ሰማይ በአራቱ ማዕዘን ያሉትን ፍጥረት አሰገዛው፤ ወአሠልጠኖ አራቱ ማዕዘን ባሉ ፍጥረት አሠለጠነው።
ወፈጠረ ሎቱ እምሥጋሁ ረድኤተ።
ከአካሉ ልትረዳው ፈጠረለት  በአቅልሎ ክበደ ዋዕይ ልጅ በማስገኘት አንድም እሱ የአፍአውን እሷ የውስጡን በማከናወን ።   
ወሰመያ ሔዋን።      
ስሟን ሔዋን አላት ፤ ሕይወት ማለት ነው እንደግብሯስ ሞት በተባለች በተገባት ነበር ሕያዋን ጸድቃን ከሷ የሚወለዱ ስለሆነ ሕይወት አላት።
ወአንበሮሙ ውስተ ገነተ ዔዶም ጽባሐዊ ።
መወደድ ባለው በምሥራቅ በኩል በገነት አኖራቸው አንድም ጽባሐዊ መወደድ ባለው በገነት ምሥራቅ አኖራቸው አራት ማዕዘን አለውና።
ወወሀቦሙ ይትፈሥሑ በኵሉ ሠናያት አምላካውያት ዘእንበለ ክልዓት።
ወሀቦሙ ዘእንበለ ክልዓት ከአምላክ በሚገኘው ነገር ሁሉ ደስ ይላቸው ዘንድ ያለመከልክል ሰጣቸው ይትፈሥሑ ዘእንበለ ክልዒት ያለመከልከል ደስ ይላቸው ዘንድ 
ወወስነ ሎሙ ትእዛዘ በእንተ አሐቲ ዕፅ ባሕቲታ
ስለ አንዲት ዕዕ ብቻ ትእዛዝ ወሰነባቸው።
ወይእቲ ዕፅ እንተ ታሌቡ ሠናየ ወእኩየ ።
ያችም ዕፅ ባይበሏት በጐ ቢበሏት ክፉ የምታስታውቅ ናት።
ከመ ኢይብልዑ እምኔሃ።
ወሰነ ከመ ኢይብል አምኔሃ ከሷ አንዳይበሉ ትእዛዝ ወሰነባቸው። ሐተታ የገዥና የተገዥ ምልክት የዓቂበ ሕግ ምልክት ጾምንም በዚህ ነገረው።
እስመ አመ ይበልዑ እምኔሃ ሞተ ይመውቱ ።
ከሷ የበሉ እንደሆነ የሞት ሞት ይሞታሉና ብሎ
ወለእመ ሰምዑ እንከ ትእዛዞ ይከውኖሙ ሕይወተ ዘለዓለም ።
ትአዛዙን ቢጠብቁ የዘለዓለም ድኅነት ይሆናቸዋል ብሎ። አንድም ትእዛዙን ጠብቀው ቢሆን የዘለዓለም ድኅነት በሆናቸው ነበር ። ወለእመሰ ተዓደው ይከውኖሙ ሞተ። ትእዛዙን ግን ቢያፈርሱ ሞት ተፈረደባቸው ። ወሶበ ርእየ ሰይጣን ዕበየ ስብሐቲሁ ወክብራቲሁ ሰይጣን የራሱን ደግ ክብሩን ፤ ደግ ጌትነቱን ባየ ጊዜ
ወብርሃነ ዘይትዓፀፍ ቦቱ ።
ተሰጥቶት የነበረውን ጸጋውን ባየ ጊዜ።
ወርእየ ርእሶ በርእሱ እምድኅረ ክብር ወሢመት ዓባይ።  
ከሹመቱ ከተሻረ ከልዕልናው ከተዋረደ በኋላ ራሱን በራሱ በመረመረ ጊዜ ወደቀ አንድም መልስ የአዳም ደግ ክብሩን ደግ ጌትነቱን ባየ ጊዜ ለአዳም የተሰጠውን ጸጋውን ባየ ጊዜ አዳም ከተሾመ ከከበረ በኋላ የራሱን ክብር በአዳም ላይ ሁኖ ባየ ጊዜ ወድቀ በድቀተ ቅንዓት።
ቅንዓት ባመጣው ድቀት ወደቀ ደንገፀ በድንጋፄ ቅንዓት ፤ ቅንዓት ባመጣው ድንጋፄ ደነገጸ  ኃዘን ባዘነ ቅንዓት ተከዘ በትካዘ ቅንዓት፤ ኃዘን ትካዝ ባመጣው ቅንዓት አዘነ ፤ ወድቀ መውዱቅ ውዱቅ ይላል መውዱቅ ዲያብሎስ ውዱቅ አዳም ነው አዳምን ያሳተ ዲያብሎስ ወደቀ ድል ሆነ።
ወቀብጸ ተስፋሁ ። ተስፋ ቆረጸ
በእንተ ዘኢፈቂዶቱ እግዚአብሔር ኪያሁ፤
እግዚአብሔር እሱን ባለመሻቱ
ወኢያግብዖ ውስተ ዘቀዳሚ መንበሩ፤
ወደ ቀደመ ቦታው ወደ ቀደመ ማዕርጉ ባለመመለሱ ወኢተርፈ ሎቱ እምነ ዘይእኅዝ ዘእንበለ ዘያሰግዶ ለብእሲ ከመ ያውጽኦ እምፈቃደ ፈጣሪሁ ። ወይም እንጂ ይመልሰኝ ይሆናል ብሎ ነበርና አዳምን ከፈጣሪው ትእዛዝ ያወጣው ዘንድ አዳምን ከሚያስትበት ግብር በቀር ከያዘው ከረዘዘው የቀረለት የለም ። 
ወነሥአ ሎቱ ተኃይሎተ ዘበእኪት።
የበጐ መበረታታት አለና የከፉ መበራታትን አደረገ።
ወመንሱተ ወልታ 
ወልታ መንሱተ ሲል ነው አዳምን ድል የሚነሳበትን ጋሻ አነገበ።
ወመጽአ መንገለ ብእሲ በውእቱ ተኃይሎት ጸዋግ በክፉ መበራታት ወደ አዳም መጣ ሐተታ ፤ አሞንዮስ አውሳብዮስ በገነት እንዳሉ ሁነው ይጽፋሉ ወአምጽእዎ ለውእቱ ንዋይ እምኢየሩሳሌም እንዳለ ነቢይ በኢየሩሳሌም ሳለ በባቢሎን እንዳለ አድርጎ በእንተ ምክንያት ዘያወፅእ ቦቱ እምገድል ሠናይት ከበጐ ግብር ስለሚያወጣበት ምክንያት እምገነት ሠናይት እምፍኖት ሠናይት እምግእዝ ሠናይት እምዕረፍት ሠናይት ይላል ። 
ወጸንሆ እንከ።  
ሸመቀበት ሰው በጠላቱ እንዲሸምቅ ጦሩን ሰንግሎ ጋሻውን ወልውሎ፤ አንድም ድል የሚነሣበትን ግብር ዐወቀ ፤ አንድም የሚለያዩበትን ጊዜ ጠበቀ ።
በከመ የአምሮን ጸላዒ ለጊዜያት ለነኒ ይደልወነ ከመ ናአምር ድካማቲነ እንዲል ። ወናሁ ውእቱ ምስለ ረድኤቱ ተሠልጡ ውስተ ኵሉ ዕፀወ ገነት።   
ተሠልጡ ካለ ውእቱ ወረድኤቱ ምስለ ረድኤቱም ካለ ተሠልጠ ቢል በቀና ነበር ልማደ መጽሐፍ ነው ሌሊት ምስለ መዓልት ይትካፈልዎ ለዘመን በዕሪና። ከንቶ ይትናገሩ ፩ዱ ምስለ ካልዑ እንዲል እሷ እሱ በገነት ባለው ዕፅ ሁሉ ሠልጥነው ነበር ።
ዘእንበለ አሐቲ ዕፅ ባሕቲታ እንተ ከልኦ እምኔሃ ።
እሷን አትብላ ብሎ ከከለከለው ካንዲት ዕፅ በቀር ወተፈሥሐ እንከ ዓቢየ ፍሥሐ  
ፈጽሞ ደስ አለው ።
ወአእመረ ከመ በውእቱ ፅዕ ይመውኦ ።
በፅፀ በለስ ድል እንዲነሣው ዐውቋልና ።
ወያወፅኦሙ ለአዳም ወለሔዋን እምፍግዓሆሙ ።
አዳምና ሔዋንን ከተድላቸው ከደስታቸው እንዲለያቸው አንድም ተድላ ደስታ ከሚያደርጉባት ከገነት እንዲያወጣቸው ዐውቋልና።
ወተኀብአ እንከ ውስተ ሥጋ ከይሲ ። 
በሥጋ ከይሲ ተሰወረ ።
ወረሰያ ምክንያተ ለኃጕል ።
ለጉዳት ምክንያት አደረጋት ታሪክ እንስሳት አራዊት ከአዳም ዘንድ ሄዱ ስለምን ቢሉ ስም ለመሰየም ስምስ ተሰይመዋል እስከዚያ ወዴት ኑረው ብሎ ለደጅ ጥናት ሄደው አርደህ ብላን አሉት ። ምን አጥቼ በገነት ባለ ፅፅ ሁሉ አሠልጥኖኛል፤ እናንተስ ባላችሁበት ያርባችሁ ያብዛችሁ ያስፋፋችሁ ብሎ መርቆ ሰደዳቸው ፤ ዲያብሎስ ከመንገድ ቆይቶ ወዴት ሂዳትሁ ኑራችኋል አላቸው ። ከአዳም ከጌታችን አሉት። አዳም ጌታችሁ ምን ይመስላል አላቸ ከፀሐይ ሰባት እጅ ያበራል አሉት በዚያውስ ላይ ይህን ያህል ደስታ ምን ተገኝቷል አላቸው ። እንዲህ ብንለው እንዲህ አለን ሞት ሲቀርልን አሉት። ያችን ዕፅ ቆርጦ ማን ካፉ ባገባልኝ ነበር ብሏል ። በሌላው ቀን ሲሄዱ አገኛቸው ወዴት ትሄዳላችሁ አላቸው። ከአዳም ከጌታችን አሉት ። አስከትሉኝ አላቸው አዳም ጌታችን መልከ መልካም ነው አንተ መልከ ጥፉ ብለው ትተውት ሄዱ ። አብርል አዝርል የሚባሉ የገነት አዕዋፍ መጡ አስከትሉኝ አላቸው። አዳም ጌታችን መልካም አንተ ክፉ ብለው ጥለውት ሄዱ ። እባብ መጣች የገመል ወሳብሬ ታህል ነበር ወዴት ትሄጃለሽ ኣላት ወደ አዳም ወደ ጌታዬ አለችው፤ አስከትይኝ አላት አዳም ጌታዬ መልካም ነው አንተ ክፉ ነህ አይሆንም አለችው ። ከፉ ከሌለ መልካም በምን ይታወቃል መስሎሻል ። በዚያውስ ላይ ባንቺ እንጂ አምር የለም ብሎ በውዳሴ ከንቱ ጠለፋት፤ አስከትላው ሄደች። ቁልቁለቱን ጨርሰው እዳገቱ ደረሱ ፤ የቆላ መንገድ እንጂ ካልተዋወቁበት አይሆንም እየተዛዘልን እንውጣው አላት እሽ አለችው። ነይ ልዘልሽ አላት ጥቂት እልፍ አድርጎ በጽሐ ሥጋ ተባርዮ ዘጾርኪኪ ጹርኒ አላት አዘለችው። በሷ ሥግው ሆነ። ከአዳም ዘንድ ሄደ ጸሎት ይዞ አገኘው አስቀድሞ በዚህ ድል ነሣው በሐከ ንጉሠ ሰማያት ወምድር አለው ፍልጥ አርዌ ምድር። ንጉሠ ምድር ነኝ እንጂ ንጉሠ ሰማያት ፈጣሪዬ ነው አለው ። ሔዋን ወዴት ናት አለው ፤ ከዚያ አለች አለው ቢሄድ ሥራ ፈትታ አገኛት በዚህ ድል ነሣት።
ወአስተርአያ ለሔዋን በነገር ጥዑም ዘምሉዕ ጕሕሉተ ክዳት ተንኮልን በተመላ ደስ በሚያሰኝ አነጋገር ሔዋንን ተናገራት ፤ በሐኪ ንግሥተ ሰማይ ወምድር አላት ደስፈቅ አላት ፤  ወይቤላ በእንተ ምንት ይቤለክሙ እግዚአብሔር ኢትብልዑ እምኵሉ ዕፀው ዘውስተ ገነት።
ለይቼ የጠየቅኋት እንደሆነ ታውቅብኛለች ብሎ በገነት ካለው ዛፍ ሁሉ አትብሉ ያላችሁ ስለምን ነው።
ወትቤሎ ንበልዕሰ እምኵሉ ዕፀው ዘውስተ ገነት በገነትስ ካለ ዕፅ ሁሉ እንበላለን፤  
ወባሕቱ ፍሬ ዕፅሰ ዘውስተ ገነት ይቤለነ እግዚአብሔር ኢትብልዑ እምኔሃ። ነገር ግን በገነት አንዲት ዕፅ አለች እሷን አትብሉ ብሎናል። 
ከመ ኢትሙቱ ሞተ።
ያው ቅሉ ነፍጎን አይደለም የሞት ሞት ትሞታላችሁ ብሎ ነው እንጂ አለችው
ወይቤላ አኮ ሞተ ዘትመውቱ።  
ጣዖቱን ይሰብካል የሞት ሞት ትሞታላችሁ ብሎ ወባሕቱ የአምር እግዚአብሔር ከመ ሶበ በላዕክሙ እምኔሃ ይትከሠታ አዕይንቲክሙ ወትከውኑ ከመ አምላክ ። በበላችሁ ጊዜ የአምላክነት ዕውቀት እንድታውቁ እንደ አምላክ እንድትሆኑ ያውቃልና፤
ወተአምሩ ከመ ሠናየ ወእኩየ
የሰውነት የአምላክነት ዕውቀት እንድታውቁ ያውቃልና ስለዚሀ ነው እንጂ የሞት ሞት ትሞታላችሁ ብሎ አይደለም።
ወአፍተዋ ከመ ትብላዕ እምውእቱ ዕፅ ዕፀ በለስን ትበላ ዘንድ አስወደዳት ልብላ ልብላ አሰኛት።
ወታብልዖ ለአዳም፤  
ለአዳም ታበላው ዘንድ    
ከመ ይኩኑ ዘየአምሩ ሠናየ ወእኩየ።
የሰውነትን የአምላክነትን ዕውቀት ያውቁ ዘንድ ፤
ወሶበ ጸነት ኀበ ነገሩ ጸንዓ ላዕሌሃ ፍትወተ ጥዕመት ምስለ ሕሊና ትዕቢት ነገሩን በተቀበለችው ጊዜ አምላክ እሆናለሁ በማለት ልብላ ልብላ የማለት ፈቃድ አደረባት። ልብላ አሰኛት።
ወአፍጠነት ወበዓልት እምይእቲ ዕፅ፤ ፈጥና ቆርጻ በላት።
ወአብልዓቶ ለአዳም፤  ለአዳምም አበላችው ። ሐተታ ነገሩን እንደ ተቀበለችው አውቆ የአምላክነት ነገር እንዲህ አይደለም የተቀዳደማችሁ እንደሆነ ያንድኛችሁ ይቀርባችኋል ለርሱ በቀኝ እጅሽ ላንቺ በግራ እጅሽ ቆርጠሽ ፩ ጊዜ ጉረሷት አላት። የሷ ሲነሣት አይቶ እሱ ያመልጠኛል የሱ ሲነሣው አይታ እሷ ታመልጠኛለች ብሎ፤ ዛሬም ሴቶች ይህ አብነት ሁኖባቸው በቀኝ እጃቸው ለባሎቻቸው እያሳለፉ በግራ እጃቸው ይበላሉ።   
ወወጽኡ እምትእዛዘ እግዚኦሙ ወተዓደው እምነገሩ።
ከፈጣሪያቸው ትእዛዝ ወጡ።
ወኮኑ ቀታልያነ ርእሶሙ
ራሳቸውን አጥፊ ሆኑ።   
ወተሰዱ እምድረ ገነት ኀበ ምድረ ሕማም፤ 
ከገነት ወደ ምድረ ፋይድ ወረዱ፤ ሐተታ ምድረ ፋይድ ማለት ምድረ ኃሣር ወመርገም ምድረ ድንጋጼ ወረዓድ ማለት ነው ።  
ወአርአያ ኅሱም ወኅሱር፤
ክፉና መልካም ቀይና ጥቁር አጭርና ረጅም ቀጭንና ወፍራም ወደሚፈጠርበት። 
ወሲሳየ ኃዘን።
ቢያገኙት ቁንጣን ቢያጡት ቀጠና ወደሚሆንበት
ወፈትሐ ላዕሌሆሙ በሞት እስከ ለዝሉፉ
አምስት ሺሀ አምስት መቶ ዘመን እስኪፈጾም
በሞተ ሥጋ ላይ ሞተ ነፍስን፤ በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ገሃነምን ፈረደባቸው።
ወእምድኅረ ተዓርቁ እምልብሰ ብርሃን ዘተአጽፉ ቦቱ። ከተሰጣቸው ከጸጋቸው ከተለዩ በኋላ  አንድም የተሰጣቸው ጸጋቸውን ባጡ ጊዜ።
ተኃፍረ አዳም እም እግዚአብሔር።
ከእግዚአብሔር የተነሳ አዳም ፈራ፤ ሐተታ ሰኰና ብአሲ እያሰማ ቢመጣ አዳም ፈርቶ ከእንጨት ውስጥ ተሰውሮ ተገኝቷል። 
በእንተ ተዓድዎቱ ።
ከትእዛዙ ስለወጻ ፈራ።
ወናሁ ቀደመ ቃል ከመ ነፍስ ነባቢት እንዘ አልቦ ዘይኴንና ወዘይኄይላ።
ተኃፍረ ብሎ ነበርና በምን አውቆ ትሉኝ እንደሆነ የሚገዛት የሚያዛት ሳይኖር ነፍስ አዋቂት እንደሆነች አስቀድሞ ተነግሯል ወገብረ ላቲ ሥልጣነ በውስቴታ ከመ ትግበር ዘከመ ኃረየት ተብሎ ወለእመሰ ነበረት በትእዛዙ እምኮነት ብርህተ በብርሃነ ትእዛዙ። ትእዛዙ ጠብቃ ኑራ ቢሆን ትእዛዙን ቢጠብቁ በሚገኝ ብርሃን ትእዛዙን በመጠበቅ ብርሃን ብርህት በሆነች ነበር ።
ወሶበ ጸነት እንከ ኀበ ተዓድዎተ ነገሩ ጸልመት በጽልመተ ተአደዎ። 
ትእዛዙን ግን ቢያፈርሱ። ትእዛዙን ቢያፈርሱ በሚመጣ ጨለማ ትእዛዙን በማፍረስ ጨለማነት ጨለመች ማለት ። ትእዛዙን ቢያፈርሱ በሚመጣ ድንቁርና ደነቆረች።
እስመ አልቦ ዘይኴንና ወዘይኄይላ በውስተ ፈቃደ በፈቃዷ የሚያዛት የሚገዛት የለምና እመ ነበረት ለበጎው የሚያዛት የሚገዛት ሳይኖር ሶበ ጸነት ለክፉው።
ወበእንተ ዝንቱ ይረክቦ ለብእሲ ገነት ፤
ገነተ ሲል ነው ፤ መገናኘት የጋራ ከሆነ ብሎ እንዲህ እለ እንጂ ። ስለዚህ አዳም ገነትን ይወርሳል ። ሶበ ተመይጠ እምእኵይ ውስተ ሠናይ ወገቢሮቱ ። ከክፉ ወደ በጎ ቢመለስ በጐውን ወደ ማድረግ ቢመለስ ገነትን ይወርሳል፤   
ወሶበ ጸነ እምሠናይ ኀበ እኩይ ወገቢሮቱ፤ ከበጎ ወደ ክፉ ቢመሰስ ክፉውን ቢያደርግ 
ደለዎ ኵነኔ
ሞት ተፈረደበት።
ወበጸኒኖቱ ለአዳም ኀበ ፈቃደ ሰይጣን ወተዓድዎተ ፈጣሪሁ ኮነ እንከ ገብሮ ለሰይጣን፤
አዳም የሰይጣንን ነገር በመከተሉ ከፈጣሪው ትእዛዝ በመውጣቱ የሰይጣን ተገዢ ሆነ። 
ወታሕተ ሥልጣኑ
ከሥልጣኑ በታች ነ፤  
ወተርፈ ውስተ ምድር ኅዙነ ወትኩዘ
በዚህ ዓለም ያዘነ የተከዘ ሁኖ ኖረ ፤ አንድም ኮነ ገብሮ ለሰይጣን ታሕተ ሥልጣነ፤ ከሥልጣኑ በታች ሁኖ ለሰይጣን ተገዢ ሆነ ። ወተርፈ በዚህም ዓለም ያዘነ የተከዘ ሁኖ ኖረ፤   
በእንተ ዘገብረ ተዓድዎተ፤    ከፈጣሪው ትእዛዝ ስለወጣ
ወዓለወ ትእዛዘ ፈጣሪሁ፤
የፈጣሪውን ትእዛዝ ስላፈረሰ፤  
ወእምንዳቤ እንተ ረከቦ።
ካገኘው ጸዋትወ መከራ የተነሣ፤   
እምኃዘን ወእምአውያት ፤     
ከኃዘን ከልቅሶ የተነሣ፤   
ወክኢወ አንብዕ ውዑይ።  
ቁጡ እንባን ከማፍሰስ የተነሣ ። ሐተታ ቁጡ እንባ ዓይን ከማጥፋት ያደርሳል ። አንድም ውዑይ እንባ ከማፍስስ የተነሣ።
ረስዓ ገነተ እንተ ነበረ ባቲ፤
የነበረባትን ገነትን ዘነጋ።
ወአልቦቱ ካልዕ ሕሊና ዘእንበለ ብካይ ላዕለ ኃጢአቱ።
በኃጢኣቱ ከማዘን ከማልቀስ በቀር ማዘን ማልቀስ ነው እንጂ ሌላ ግዳጅ አልነበረውም ፤ ሐተታ አዳምን የቤተ ፈት ልማድ አላገኘውም ቤተ ፈት በዚህ ጊዜ እበላ እጠጣ እለብስ አጌጥ የነበረ ቀረብኝ ብሎ ያዝናል ፤ እሱ ግን የማይገባ ሥራ ሠርቼ ፈጣሪዬን አሳዘንሁት ብሎ ነው እንጂ በገነት ሳለሁ አደርገው የነበረው ተድላ ደስታ ቀረብኝ ብሎ አይደለምና በኃጢአቱ ከማዘን ከማልቀስ በቀር በኃጢአቱ ማዘን ማልቀስ ነው እንጂ ግዳጅ አልነበረውም አለ፤
ወአእመረ እግዚአብሔር ይትለዓል ዝክሩ ንስሐሑ ወገዓሮ ብዙኃ ወምንዳቤ እንተ ረከቦ ተሣሃለ ላዕሌሁ ወምሕሮ ። 
በልብ መታስቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና አላበጀሁም ማለቱን ብዙ መጨነቁን ጸዋትወ መከራውን አይቶ ይቅር አለው አዘነለት፤  
ወፈቀደ ያድኅኖ እምዳኅጹ በእንተ ፪ ገጻት ።
ስለ ሁለት ነገር ከፍዳው ሊያድነው ወደደ፤ 
፩ዱ በእንተ ንስሐሑ ፤  
ከሁለቱ አንዱ አላበጀሁም በማለቱ ነው፤ 
ወገዓረ ብካዩ ለኃሢሠ ሥርየት ፤
ኃጢአቱ ሊሠረይለት ኃጢአቱን ሊያሥተሰርይለት እያለቀሰ በመጨነቁ ነው።
ወረሲኦቱ ገነተ ወፍግዓሁ ወተድላሁ፤  
ገነትን በመዘንጋቱ ተድላው ደስታውን በመዘንጋቱ ነው።
ካልዕሰ በእንተ ዘተትሕተ ውእቱ ተትሕቶተ።
ወካልዕሂ ሲል ነው ሁለተኛውም እሱ ፈጽሞ ስለተዋረደ ነው ።
ወዓዲ አጥረየ ሰይጣን መዊዓ ወኃይለ ላዕለ አዳም ወቀነዮ
ዳግመኛ ሰይጣን በአዳም ላይ ኃይልን መዊዕን ገንዘብ እደረገ ።
ወኮነ ጼዋሁ ምርኮው ሆነ።
ወኵሉ ዘርዑ ምስሌሁ ፤
ልጆቹም ከሱ ጋራ እንደሱ ተገዙ።
ወተሰልጠ ሰይጣን ዲቤሆሙ ለአስግዶ በብዙኅ ግብራት። አሳታቸው ብሎ ነበርና ዳግመኛ በብዙ ነገር ለማሳት ሰይጣን ሠለጠነባቸው። 
ወመንክራት ትልዋት ፤
ቀጽሎ ቀጽሎ በሚደረግ በምትሐት ተአምራት ፤ አንድም ወመንክራት ትልዋት ይላል ። ቀጽሎ ቀጽሎ አራድፎ አራድፎ በሚመጣ መከራ ሠለጠነባቸው። ወቦ እምኔሆሙ ዘመሐረ ከመ ፍጥረት ተፈጥረት እምኀበ ርእሳ ባሕቲታ ዘእንበለ ሠራዒ ወገባሪ ። ከርሳቸው ወገን ፍጥረት ያለ ሠራዒ ያለ መጋቢ ከባሕርይዋ እንደ ተፈጠረች ያስተማረ አለ እነ ማኒ ወቦ እምኔሆሙ ዘመሐረ ከመ ፀሐይ ወወርህ ወከዋክብት እሙንቱ እለ ፈጠሩ ዓለመ፤ ሰማይ ምድርን የፈጠሩ ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት እንደሆኑ ያስተማራቸው አሉ ጽርዓውያን ፀሐይ ጨረቃን ሰባቱን ከዋክብት ያመልኩ ነበር ። ወቦ ዘመሐረ ከመ አምልኮ አራዊት ወእንስሳ ይእቲ ፍኖት በአማን ጥይቅት፤ አምልኮተ አራዊት አምልኮተ እንስሳ በውነት የተረዳች ሃይማኖት እንደሆነች ያስተማራቸው አሉ ።
ወባቲ ይትረከባ ፈቃዳት ።
የሚሹት ነገር በሷ እንዲገኝ ።
ወይትፌጸማ ባቲ ስእለታት ።
ልመናም በሷ እንዲገኝ ያስተማራቸው አሉ ። ሐተታ ግብጻውያን ላም ያመልኩ ነበር ባቢሎናውያንም ዘንዶ ያመልኩ ነበር፤ 
ወአርስኦሙ አግዚአብሔርሃ አምላኮሙ ።
ፈጣሪያቸው እግዚአብሔርን አስካዳቸው ።
ወቦኡ ውስተ ልጎተ ርስአት፤ ወደ ፍጹም ዝንጋኤ ገቡ ፤
ወተመንኖት ወተቀንዮት ለብዙኅ ኃጢአት ዘዘዚአሁ
ልዩ ልዩ የሚሆን ለብዙ ኃጢአትም ወደ መገዛት ወደ መናቅ ገቡ ።
እምቅትለት፤  ነፍስ ከመግደል ወገን
ወእምዝሙት ወሐሰት ወሐሜት ።
ከዝሙት ከሐሰት ከሐሜት ወገን አንዱ ብቻ ሠርቶት አይቀርምና በከፊል ተናገረው።
ወአምዖት ። 
ሰውን እግዚአብሔርን ከመበደል ወገን፤
ወትዕግልት  ከቅሚያ ወገን
ወአምልኮተ ጣዖት ዘግብረ እድ
የሰው እጅ ሥራ የሚሆን ጣዖትን ከማምለክ ወገን
ወክሂደ እግዚአብሔር ፤ 
እግዚአብሔርን ከመካድ ወገን ።
ወዘይመስሎ ለዝንቱ ።  
ነሣሣለትና ይህን ከመሰለ ወገን ለብዙ ኃጢአት ወደ መገዛት ገቡ።
ወኮኑ ስይጣናት ውኩላነ ፤
ስይጣናት ቁራኞች ሆኑ ። 
ወሥሉጣነ በአዳም ወበኵሉ ዘርዑ ውስተ አሕጉሎ
በአዳም በልጆቹም ሁሉ በቁራኝነት የሠለጠኑ ሆኑ
ከመ ጺዉዋን
ምርኮኞች እንደመሆናቸው ፤ አንድም ማራኪ በምርኮኞቹ እንዲሠለጥን ።   
ወለዘሞተ እምኔሆሙ የአሥሩ ነፍሶ ውስተ ሲኦል
ይህም ሊታወቅ ከሳቸው ወገን የሞተውን ሥጋውን በመቃብር ነፍሱን በሲኦል በገሃነም ተቈራኝተው ይኖሩ ነበር ። አሜሃ ይትፌነዋ ነፍሳት ውስተ ገሃነም እስከ ይመልአ አብያተ ሞት እንዲል ።
ወኮነ ቦሙ ዝንቱ ግብር ለዝሉፉ እስከ ተፍጸሜተ
፶፻ ወ፭፻ ዓመት እምፍጥረቱ ለአጻም። አዳም ከተፈጠረ ጀምሮ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ቁራኝነት ፈጽሞ ተደረገባቸው ።   
ይቆየን
****************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
04/06/2011 ዓም

No comments:

Post a Comment