Thursday, February 7, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 3


===================
ወአሠርቱ አቅማራት ።
ዐሥሩን ሰንጠረዥ መጻፍንም እንጀምራለን፡፡ አንድም ሰንጠረዥን መቅድም አድርግ ፤ የአራቱ ወንጌል መቅድም የሚሆን ዐሥሩ ሰንጠረዥ መጻፍን እንጀምራለን ፤ አንድም ጽሒፍን አውርድ፤ ጽሒፈ መቅድመ ፲ቱ አቅማራት ፤ የዐሥሩ ሰንጠረዥ መቅድም የሚሆን ሰባቱን ክፍል መጻፍን እንጀምራለን፡፡ ሐተታ ምኑናት መጻሕፍተ ዕዳ መጻሕፍተ ደብዳቤ አሉና ከዚያ ሲለይ ክቡራት አለ ፤ ርኩሳት መጻሕፍተ ጥንቆላ አሉና ከዚያ ሲለይ ንጹሐት አለ፡፡
በሰላመ እግዚአብሔር አብ አሜን።
እግዚአብሔር አንድ ቢያደርገን፤ ሐተታ። አእለፈ እስራኤል አንድ ቢያደርጋቸው ንሴብሖ እንዳሉ፤ ሠለስቱ ምእት ሊቃውንት ነአምን በ፩ዱ አምላክ እንዳሉ ።
ወእምድኅረ ዝንቱ፤ 
በሰላመ እግዚአብሔር አብ ብሎ ነበርና እግዚአብሔር አብ አንድ ካደረገን በኋላ አንድም ንቀድም በረድኤተ እግዚአብሔር ብሎ ነበርና በእግዚአብሔር እጋዥነት ከጀመርነ በኋላ፤ አንድም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ ነበርና በሦስቱ ስም ካመንን በኋላ።  
ይሤኒ ዘይቀድም መቅድመ ነገር ፍሡሕ፤ 
ዘይቀድምና መቅድም አንድ ወገን፤ ነገር  ወንጌል ናት ሥነዜና ለዘለዓለም እንዲል፤ ፍሡሕ አላት፤ ወጻድቃንሰ ውሰተ ሕይወት ዘለዓለም ትላለችና የወንጌልን መቅድም መጻፍ ይመቻል። አንድም እየራሱ ለማውጣት የወንጌልን የመቅድሙን መቅድም መጻፍ ይመቻል።
ወይትከሠት ቦቱ አንብቦቱ ርቱዕ።
የቀና መመልከቱ የሚገለጽበት።
አኮቴት ለእግዚአብሔር።
ክብር ይግባውና። ሠዋሪ።
ባሕርዩን በባሕርዩ የሚሠውር ሥውር ብከ ዕበይከ ለሊከ ብከ ተከደንከ ወለሊከ ኪያከ አንጦላዕከ እንዲል፤ አንድም ትዱሳንን በክብር የሚሠውር ወይሤውር ኅሩያነ በደመና እንዲል፤ አንድም ጻድቃንን ከመከራ የሚሠውር እስመ ሠወርከነ ወረዳእከዕነ እንዲል።    ወከዳኒ።
በነፍስ በሥጋ ከባቴ አበሳ። 
ነባቢ ቃል። ወከሃሊ።
አካላዊ። አንድም ነባቢ ለይኩን ለይኩን ብሎ የተናገረ ወከሃሊ፤ ያንኑ ማድረግ የተቻለው ሐተታ። እሱ ተናግሮት ሳይደረግ የቀረ የለምና ወእምከመ ወጽአ ቃል ይትገበር ግብር እንዲል። አንድም ነባቢ እወርዳለሁ እወለዳለሁ ብሎ ያናገረ፤ ወከሃሊ ያንኑ ማድረግ የተቻለው። አንድም ነባቢ ሰማይ ወምድር የኃልፍ ብሎ የተናገረ ወከሃሊ ያንኑ ማድረግ የሚቻለው ። ሕያው።
ሕያው ለራሱ ፤   ወማኅየዊ።
ማኅየዊ ለሌላው፤  ወመዋኢ።
መዋኤ ኃጢአት እስመ ንጹሐት ጠባይዓቲሁ ለእግዚአብሔር ዘእንበለ ነውር እንዲል ፤ እንድም መዋኤ ሥርዓት ወያፈልስ ሥርዓተ ውስተ ሥርዓት እንዲል እምሥርዓትም ይላል ። አንድም መዋዔ ሕሊናት እስመ ሕሊና ይደክም ወየሐጽር እምአእምሮተ እግዚአብሔር እንዲል።
ዘአንቅሐ አልባቢነ ኀበ ዝክሩ።
በልብ ወደመታሰቡ በቃል ወደመነገሩ ልቡናችንን ያነቃቃ፤    
ወመርሐ ልሳናቲነ ኀበ አኮቴቱ ወስብሐቲሁ ።
እሱን ፈጽሞ ወደማመስገን አንደበታችንን መርቶ ያደረሰ። አኮቴተ ስብሐቲሁ ይላል ጌትነቱን ወደማመስገን አንደበታችንን መርቶ ያደረሰ ።
ንሰብሖ እንከ በእንተ ዘወሀበነ እምነ ሠናያተ ኂሩቱ በቸርነቱ ከሚገኝ ከበጐ ነገር ወገን ስለሰጠን እናመስግነው ። ሐተታ ሠናያት ያለው ልጅነት ነው ሀብትኬ መንፈስ ቅዱስ ውእቱ እንዲል። 
ወናእኩቶ እንበይነ ዘጸገወነ እምዕበየ ጸጋቲሁ በለጋስነቱ ከሚሰጠው ክብር ወገን ስሰሰጠን እናመስግነው ዕበየ ጸጋ ያለው ልጅነትን ገንዘብ አድርጎ እስከ ከዊነ እሳት ያለው ማዕርግ ነው።
ወንቀድስ ስሞ ክቡረ ቀድሶቶ ድልወ።  
ክቡር ስሙን የሚገባ ምስጋና እናመስግነው። ሐተታ ባንድነቱ ምንታዌ በሦስትነቱ ርባዔ ሳንቀላቅል ። አንድም ሰውን ጻድቅ ቢሉት ሐሰት፤ ባዕል ቢሉት ንዴት ኃያል ቢሉት ድካም ይስማማዋል እሱ ግን ጻድቅ ዘአልቦ ሐሰት።  ባዕል ዘአልቦ ንዴት ኃያል ዘአልቦ ድካም ነውና።   
በእንተ ዘከሠተ ለነ እምነ ምሥጢራተ ሃይማኖት በተዋሕዶተ ባሕርዩ ለሊሁ። ከሠተ ለሊሁ በባሕርይ አንድ መሆኑን ከማመን ምስጢር ወገን ስሰገለጸልን እናመስግነው  ሐተታ በከፊል ተናገረ የወጣኒ የማዕከላዊ የፍጹም አለና። ቦኑ እምነቶሙ ክመ እምነተ አብርሃም እንዲል።
ወትሥልስተ አካላቲሁ። 
በአካል ሦስት መሆኑን። ወገጻቲሁ በቅርጽ፤ ወመልክዑ በገጽ፤   ወአሳሪሁ አንድ አድራጊውን ከማመን ምሥጢር ወገን ስለገለጸልን እናመስግነው ወአሠረ ፪ተ ሕላዌያተ እንዲል።
በእንተ ዘወሀበነ ቦቱ።   
ኪያሁ ሲል ነው አብ ቢሉ ልጁን ስለሰጠን ወልድ ቢሉ አካሉን ለተዋሕዶ ሰለ ሰጠልን ሥጋውን ደሙን ስለ ሰጠን፤  
ወበእንተ ዘአዕተተ እምኔነ ኩሎ ምግባረ ዕልወታት በዘአምጽአ ቦቱ ውስተ ወንጌሉ ቅዱስ።
ሰው ሁኖ በሠራት በወንጌል ዘአምነ ወዘተጠምቀ ይድኃን ባለው ኢትጥአምን ኢትልክፍን ስለአሳለፈልን። አንድም አዳምና ሔዋን ያመጡትን ፍዳ ስለአራቀልን ፈጽመን እናመስግነው። በግብራቸው ዕልወታት አላቸው።
ወቦቱ አስተርአየት ተአምራቲሁ ድውይ መፈወሱ።
ወተከሥተት መንክራቲሁ ጋኔን ማውጣቱ።
ወኃይላቲኒሁ። 
ሙት ማንሣቱ የተገለጸችበት።
ወስብሐት ሎቱ   ክብር ይግባውና።
ይዕበይ ክብሩ።
ጌትነቱ ይክበር ይመስገንና።
ወይትለዓል ዝክሩ።  
በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና።
ወፍጽምናሁ።
ሕልውናው አንድነቱ ከፍ ከፍ ይበልና። 
ወምስለ ዝንቱ ኩሉ ከመ እስትጉቡእ ዘይትፈቀድ ኀበ ጥያቄሃ ወፈቂድ ኀቤሃ ውስተ ኩሉ መጽሐፍ ፯ቱ ይህም ይህ ነው ከዚህ ጋራ በዚህ ላይ እሷን ከሹዋት ከመረመሯት ዘንድ ልቡና የሚሻው ነገር ሁሉ እንደ ተሰበሰበ ሁኖ አለ ጸውዓተኒ ማንሻ ።
አንድም ይህም ይህ ነው ከዚህ ጋራ በዚህ ላይ እሷን ከሹዋት ከመረመሯት ዘንድ ልቡና የሚሻው ነገር ኩሉ በሰባቱ ክፍል እንደተሰበሰበ ሁኖ እሷን በጽሕፈት ወደ መሻት ወደ ማሰብ ማለት እሷን ወደ መጻፍ።
ወናሁ ጸውዐተኒ መፍቅድ ኀበ ኃሢሠ ዘክሮታ ።
እሷን በጽሕፈት ወደመሻት ወደማሰብ ፈቃደ ንጉሥ ፈቃደ ነፍስ ፈቃደ መንፈስ ቅዱስ አነሣሣችኝ፡፡ መፍቅድ ዐፀባ ይላል አብነት ቁርጽ ፈቃድ ፤ የላይ ቤት አማርኛ እገባሪ ፈቃድ።
ወጽሕፈቱ ውስተ ዝንቱ መጽሐፍ ንጹሕ ከመ ይኩን ብጽሐተ ለረባሕ፡፡ ከፈቃደ ሥጋ ንጹሕ በሚሆን በወንጌል እጠግብ ይህ መቅድም መጻፉ ለወንጌል መዳረሻ ሊሆን ነው ሐተታ። ይህማ በሌላ ተጽፎ ተምረውት ቢገቡ ይከለክለናልን ብሎ  ጽሕፈቱ በዝንቱ ከፈቃደ ሥጋ ንጹሕ የሚሆን የመቅድም መጻፍ ለወንጌል መዳረሻ ልሆን ነው።
ወመርሐ ለዘየኃሥሦ ዘይትፈቀድ። የሚወደደው የሚሻው ምሥጢር ለሚሻ ደቀ መዝሙር መርህ ሊሆን ነው።
ወዛቲ ይእቲ ግብር ቀዳማዊ። ይህ ነው መጀመሪያውን ግብር ቀዳማዊ ብለውታል፡፡ ግብር ቀዳማዊ ይባላል ።
ወካልዑ በቁዔት ። ሁለተኛውን በቁዔት ብለውታል በቁዔት ይባላል ወዳግሙ ይላል ።
ወሣልሱ ሥርዓት ሦስተኛውን ሥርዓት ብለውታል ሥርዓት ይባላል
ወራብዑ ስም አራተኛውን ስም ብለውታል ስም ይባላል፡፡ ሰምዮት ትእምርት ይላል አብነት ።
ወኃምሱ መሠረት ። አምስተኛውን መሠረት ብለውታል መሠረት ይባላል እምአይቴ ይላል አብነት። 
ወሳድሱ ምስማክ። ስድስተኛውን ምስማክ ብለውታል ምስማክ ይባላል፡፡
ወሳብዑ አርእስተ ነገር። ሰባተኛውን ክፍለ ነገር ብለውታል ክፍለ ነገር ይባላል ።
ግብር ቀዳማዊ መጀመሪያውን ግብር ቀዳማዊ ብለውታል ግብር ቀዳማዊ ይባላል፡፡ አያይዞ ለመንገር ደገመው።
ወግብሩሰ ለዝንቱ መጽሐፍ ማሕየዊ ። ማሕየዊ የሚሆን የዚህ የመጽሐፍ ሥራው። ከመ ይርባሕ ቦቱ ሕይወተ ሕይወት ዘለዓለም ለደቂቀ ዕጓለ እመሕያው ። ጌታ ለደቂቀ ዕጓለ እመሕያው የዘለዓለም ድኅነትን ያስገኝበት ዘንድ ፤ ደቂቀ ዕጓለ እመሕያው የዘለዓለም ደኅንነትን ያገኙበት ዘንድ ነው  ለደቂቀ ዕጓለ እመሕያው የዘለዓለም ድኅነት ይገኝበት ዘንድ ነው፡፡
ወበጺሖቶሙ ኀበ ፈጣሪሆሙ። 
ወደፈጣሪያቸው መድረሳቸውን ፤ ተላጽቆቶሙ ከፈጣሪያቸው ጋራ አንድ መሆናቸውን  ተመስሎቶሙ ፈጣሪያቸውን መምሰልን ያገኙበት ዘንድ ነው፡፡ ሁሉንም ያስተረጐማል ። በቃል ባነጋገገር፤
ወበምግባር
በሥራ ሁለት አርእስት ተናገረ ለሁለቱም ያመጣል በቃልስ እስመ ውእቱ ይጼውዕ ወይስሕብ ኀበ አእምሮተ እግዚአብሔር ።   
በቃል ያልሁት እግዚአብሔርን ወደማወቅ ያደርሳልና ስለዚህ ነው ።
ይትባረክ። ይክበር ይመስገንና ።
ወይትለዓል ዝክሩ፡፡  
በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና፡፡
በተዋሕዶተ ባሕርዩ።   በባሕርይ አንድ መሆኑን።
ወመለኮቱ ።
በአገዛዝ በጌትነት አንድ መሆኑን ።
ወትሥልስተ አካላቲሁ፡፡   
በአካል ሦስት መሆኑን።   
ወገጻቲሁ።   በገጽ።
ወመልክኡ።  በቅርጽ ሦስት መሆኑን ።
ወአሣሪሁ።
አንድ አድራጊውን ወደማወቅ ያደርሳልና ስለዚህ ነው  ወአሠረ ፪ተ ህላዌያተ እንዲል።
ወያጤይቅ ተሥጉተ ፩ዱ ሕላዌ እም፫ቱ ሕላዌያት ከሦስቱ አካላት የአንዱን አካል ሰው መሆኑን ያስረዳልና ስለዚህ ነው።
ወተዋሕዶቶ በዘተሰብአ ቦቱ ።
ከተዋሐደው ሥጋ ጋራ አንድ አካል አንድ ባሕርይ መሆኑን ያስረዳልና ስለዚህ ነው፡፡ 
ወይዜኑ ኅዳጠ በተሐውሶቱ ወበአንሶስዎቱ ውስተ ዓለም እምጊዜ ልደቱ እምቅድስት ድንግል ንጽሕት እስከ ጊዜ ተንሥኦቱ ወዕርገቱ ውስተ ሰማያት ንጽሕት ከምትሆን ከእመቤታችን ከተወለደ ዥምሮ እስከሚነሣበት እስከሚያርግበት ድረስ በዚህ ዓለም ሠላሳ ሦስት ዓመት ከአራት ወር ከዐሥር ቀን መኖሩን ያስረዳልና ስለዚህ ነው።
ወበምግባርሰ፤ 
ቃል ላለው ጨርሶ ምግባር ላለው አመጣ በምግባርም ያልሁት።      
እስመ በተግሣጻቲሁ ልዕልት ይወስድ ኀበ ምግባራት ሠናያት ወፍጹማት ወመሥመርያት።
አንሰ እብለክሙ ባለው ፍጹማት ወደሚሆኑ ምግባራት ያደርሳልና ስለዚህ ነው ።
ወገድል ትርፍት ወክብርት። 
ፍጽምት ክብርት ወደምትሆን ወደገድለ ልቡና ያደርሳልና ስለዚህ ነው።
ወበኪዳኑ እንተ ጸርሐ ባቲ ወይቤ እመቦ ዘዐቀበ ቃልየ ይገብር ግብረ ዚአነ እገብር ወዘየዓቢ እምኔሁ ይገብር ።      
እመቦ ዘዓቀበ ቃልየ ባለው ወበአስፍዎተ ኪዳኑ ይላል አብነት በወንጌል እመቦ ዘዓቀበ ቃልየ ባለው ያደርሳልና ስለዚህ ነው።
ወዓዲ ትከውኖ ሕይወተ ዘለዓለም፤
ዳግመኛ በዚህ ዓለም ብቻ ተአምራት አድርጋለት እንደ ጋን መብራት ሁናበት አትቀርም በወዲያው ዓለም የዘለዓለም ድኅነትን ታሰጠዋለች ።  
ወዘክሡትሰ
በዚህ ዓለም ብቻ ተአምራት አድርጋለት እንደ ጋን መብራት ሁናበት እንዳትቀር በወዲያውም ዓለም የዘለዓለም ድኅነትን እንድታሰጠው የሚያስታውቅ የሚያስረዳ ነገር ። ላዕለ እለ ገብሩ ትእዛዞ አስተርእየት ላዕለ እደዊሆሙ ተአምራት ወመንክራት ወኃያላት ዓቢያት፤
ላዕለ እደዊሆሙ ለእበለገብሩ ትእዛዞ ፤ ሕጉን በፈጸሙ በሕጉ በጸኑ በሐዋርያት ቃል በሐዋርያት ቃል ሥልጣን ጋኔን ማውጣት ሙት ማንሣት ተደረገ።  
እስከ ውእቶሙ ከሠቱ እዕይንተ ዕውራን 
ዕውራንን እስከ ማብራት ደርሰው እስመ  ውእቶሙ ከሠቱ ዕውራነ። ዕውራንን አብርተዋልና ።
ወአንጽሑ እለ ለምጽ፡፡  
ልሙጸንን እስከማዳን ደርሰው አድነዋልና ።
ወሞእዎ ለሞት ።  
ሞትን ድል እስከ መንሳት ደርሰው ድል ነስተውታልና ፤ ሐተታ ሞእዎ አለ ቢያም ይፈውሱበታል ቢገድል ያሥነሡበታል ኃጠአት ቢሠራ ስርየት ይሰጡበታልና ፤       
ወከብረት ነፍሶሙ በውስተ ዓለማት ፪ኤቲ ዘዝየ ወዘከሐ፡፡   
ሰውነታቸው በወዲህም በወዲያም ዓለም ከበረች ሐተታ ፤ በወዲህ አማልክት ተመሰሉ ሰብአ ወወረዱ ኀቤነ ብለዋቸዋል፤ በወዲያውም ወሀሎ ይትዌሰኩ ሥነ በዲበ ሥን ይለዋል ።
ወአምፍርሃተ ቃሉ ርኀቁ ጸድቃን እምነ ምግባራት ምኑናት ወፍትወተ ዓለም ርኅቀተ ጥቀ ። ወይወድይዎሙ ውስተ እቶነ እሳት ያለውን ነገር ከመፍራት የተነሣ ጻድቃን ከዓለማዊ ግብር ፈጽመው ተከለከሉ  አንድም ወበፍርሃተ ቃሉ አርኃቀ ይላል ። ወይወድይዎሙ ውስተ እቶነ እሳት ባለው ነገር ጌታ ጻድቃንን ከዓለማዊ ግብር ፈጽሞ ከለከለ አንድም ወፍርሃተ ቃሉ ይላል ፤ ወይወድይዎሙ ውስተ እቶነ እሳት ያለውን ነገር መፍራት ጸድቃንን ከዓለማዊ ግብር ፈጽማ ከለከለች  አንድም ቃሉ ባለው በቀሉ ይላል ዕፄሁ ዘኢይነውም ወእሳቱ ዘኢይጠፍእ ያለውን ነገር ከመፍራት የተነሣ ጻድቃን ከዓለማዊ ግብር ፈጽመው ተከለከሉ፡፡  አንድም እንዲህ ባለው ነገር ጌታ ጻድቃንን ፈጽሞ ከለከለ ፤ አንድም እንዲህ ያለውን ነገር መፍራት ጻድቃንን ከዓለማዊ ግብር ፈጽማ ከለከለች፡፡
ወተግኅሡ እምነጽሮታ ወዘክሮታ ፤ 
በዓይን ከማየት በልብ ከማሰብ ፈጽመው ተከለከሉ፡፡
ወጸርየት አልባቢሆሙ ። ሰውነታቸው እንይ ፀሐየ ፊላ ማለት ፀሐይ እንደወደቀበት ዕንቁ ጸራችላቸው። ወተጠበበት ሕሊናሆሙ ልቡናቸው ተራቀቀችላቸው ።
እስከ በጽሑ ኀበ ሥርዓት ዘመላእክት ፤ ወደ መላእክት አነዋወር እስኪደርሱ ድረስ፡፡ ወበተግሣጸቲሁ አንሰ እብለክሙ ባለው ወበተካይዶቱ እመቦ ዘዓቀበ ቃልየ ባለው ወበነጊሮቱ፡፡  
ወጸድቃንስ ውስተ ሕይወት ዘለዓለም
ረሰዮሙ ለደቂቀ ዕጓለ እመሕያው ተመሳልያነ ኀበ ፈጣሪሆሙ ። ደቂቀ ዕጓለ እመሕያው ፈጣሪያቸውን እንዲመስሉ ልጹቃነ  ከፈጣሪያቸው ጋራ አንድ እንዲሆኑ። ብጹሕነ ወደ ፈጣሪያቸው እንዲደርሱ አደረጋቸው፤ ከመ ይግበሩ ምግባራቲሁ ወይረሱ መንግሥቶ ሥራውን ሠርተው ክብሩን ይወርሱ ዘንድ።
 ፪ተኛ ጉባኤ።
ወካልዑ በቁዔት ።
ይቆየን፡፡
 ****************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
30/05/2011 ዓም

No comments:

Post a Comment