Thursday, April 25, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 75

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
                   ******   
፳፫፡ ወሶበ ይሰድዱክሙ እምዛቲ ሀገር ጕዩ ውስተ ካልዕታ።
                   ******   
፳፫፡ ከአንዱ አገር አስወጥተው ቢሰዷችሁ ወደ አንዱ አገር ሽሹ፡፡
አማን እብለክሙ ኢይትፌጸማ አኅጉረ እስራኤል እስከ ሶበ ይመጽእ ወልደ አጓለ እመሕያው
ከአንዱ ወደ አንዱ ስንል ያለ ክብር መቅረታችን አይደለምን ትሉኝ እንደሆነ። ወልደ እጓለ እመሕያው እስኪመጣ ማለት እኔ መጥቼ እስካድርባችሁ ድረስ የእስራኤል ዘነፍስ አገር አትፈጸምም ብዬ እንዳትፈጸም በእውነት እነግራችኋለሁ።
አንድም ምድረ እስራኤል ጸባብ ናት በስምንት ቀን ትፈጸም የለምን ትሉኝ እንደሆነ ወልደ እጓለ እመሕያው እኔ እስክመጣ ጠባቢቱ ምድረ እስራኤል ቅሉ እንዳትፈጸም በእውነት እነግራችኋለሁ
                   ******   
፳፬፡ አልቦ ረድእ ዘየዓቢ እምሊቁ፡፡ ሉቃ ፮፥፵፡፡ ዮሐ ፲፫፥፲፮፡፡ ፲፭፥፳፡፡
                   ******   
፳፬፡  በዚያውም ላይ ከመምህሩ የሚበልጥ ደቀ መዝሙር የለም።
ወኢገብርኒ ዘየዓቢ እምእግዚኡ።
ከጌታውም የሚበልጥ ባሪያ የለም ከሳኦል ዳዊት ከሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስ ይበልጡ የለምን ቢሉ የኒያ መብለጣቸው ሳሉ አይደለም።
                   ******   
፳፭፡ መጠኑ ለረድእ እምከመ ኮነ ከመ ሊቁ።
                   ******   
፳፭፡ የደቀ መዝሙር መጠኑ እንደ መምህሩ ቢሆን ነው እንደ መምህሩ ቢሆን እንጂ ነው እንደ መምህሩ ቢሆን በጎ ነው። እንደ መምህሩ ቢሆን መጠኑ ነው ወለገብርኒ ከመ እግዚኡ የባሪያም መጠኑ እንደ ጌታው ነው እንደ ጌታው ቢሆን ነው እንደ ጌታው ቢሆን እንጂ ነው፤ እንደ ጌታው ቢሆን መጠኑ ነው።
ወሶበ ኮነ ለበዓለ ቤት በብዔል ዜቡል እፎ ፈድፋደ ለሰብአ ቤቱ አምጻኤ ዓለማት ፈጣሬ ዓለማት እኔን በብዔል ዜቡል ያወጣቸዋል ካሉኝ እናንተንማ እንደምን አይሏችሁ።
                   ******   
፳፮፡ ኢትፍርህዎሙኬ እንከ። ማር ፬፥፭፡፡ ሉቃ ፰፥፲፯፡፡ ፲፪፥፪፡፡
                   ******   
፳፮፡ አትፍሯቸው።
እስመ አልቦ ክዱን ዘኢይትከሰት ወአልቦ ኅቡዕ ዘኢይትዓወቅ።
የማይገለጽና የማይታወቅ የለምና ማለት የናንተ ተርታነት የነሱ ደግነት ሳይገለጥ አይቀርምና።
                   ******   
፳፯፡ ዘነገርኩክሙ በጽልመት ንግርዎ በብርሃን ።
                   ******   
፳፯፡ በጨለማ የነገርኋችሁን በብርሃን አስተምሩት።
ወዘኒ አልኆሰስኩ ውስተ ዕዝንክሙ ስብክዎ በዲበ አንሕስት
በጆሮዋቸሁ የነገርኋችሁን በሰገነት ወጥታችሁ አስተምሩት፤
(ሐተታ) ለመቶ ፳ ሰው ማስተማሩን በጨለማ በጆሮ መናገር ብሎ እንዲህ አለ።
አንድም ልጅነት ሳታገኙ የተማራችሁትን ልጅነት አግኝታችሁ አስተምሩት ልዕልና ነፍስ ሳታገኙ የተማራችሁትን ልዕልና ነፍስ አግኝታችሁ አስተምሩ።
                   ******   
፳፰፡ ኢትፍርህዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ።
                   ******   
፳፰፡  በሥጋችሁ የሚገድሏችሁን አትፍሯቸው
ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ
ነፍሳችሁን መግደል አይቻላቸውምና ።
ወባሕቱ ፍርህዎሰ ለዘእምድኅረ ቀተለ ዘቦ ሥልጣን ወይክል ነፍሰኒ ወሥጋኒ ኅቡረ አኅጕሎ በውስተ ገሃነም።
መፍራትስ ከገደለ በኋላ ነፍስና ሥጋን አዋሕዶ አሥነሥቶ በገሃነም ፍዳ ያመጣ ዘንድ ሥልጣን ያለው እሱን ፍሩት።
                   ******   
፳፱፡ አኮኑ ፪ቲ አዕዋፍ ይሰየጣ ለ፪ኤ ጸሪቀ አሶርዮን። ፪፡ነገ ፲፱፥፲፩። ግብ ፳፯፥፴፬።
                   ******   
፳፱፡ እንዲህማ ከሆነ ወድቀን ወድቀን መቅረታችን አይደለም ትሉኝ እንደሆነ፡፡ ሁለት አዕዋፍ በሁለት ሻሜ መሐልቅ ይሸጡ የለምን አሶርዮን የገበያ የሚዛን ስም።
ወአሐቲ እምኔሆን ኢትወድቅ ውስተ ምድር ዘእንበለ ያአምር አቡክመ ሰማያዊ።
ሰማያዊ አባታችሁ ሳያውቅ ከሁለቱ አንዲቱ አትጠፋም በወጥመድ አትያዝም።
                   ******   
፴፡ ወለክሙሰ ስእርተ ርአስክሙኒ ኵሉ ኍሉቊ ውእቱ።
                   ******   
፴፡ እናንተስ የራሳችሁ ፀጕር ሳይቀር የተቈጠረ ነው የተቈጠረ እንዳይጠፋ አትጠፉም።
                   ******   
፴፩፡ ኢትፍርኁኬ እስመ እምብዙኅ አዕዋፍ ትኄይሱ አንትሙ
                   ******   
፴፩፡ ከተፈጥሮተ አዕዋፍ ተፈጥሮተ ሰብእ ይበልጣልና አይዟችሁ።
አንድም አኮኑ ብለህ መልስ በኦሪት በነቢያት ያሉ ሰዎች በሃይማኖት በጥምቀት ይኖሩ የለምን ወአሐቲ እምኔሆን። በኦሪት በነቢያት ከአሉ ሰዎች ሰማያዊ አባታችሁ ሳያውቅ አንዱ አይጠፋም፤ ወለክሙሰ የናንተስ ደቀመዛሙርቶቻችሁ ሳይቀሩ የተቈጠሩ ናቸው ሥእርት አላቸው አርድእትን ፀጉር የራስ ጌጽ እንደሆነ ደቀ መዝሙር ለመምህሩ ጌጽ ነውና ፀጉር ያደገው ሲወድቅ ያላደገው ሲወጣ ደስ እንዲያሰኝ ደቀ መዝሙር ያጠናው ሲወጣ ያላጠናው ሲገባ ደስ ያሰኛልና ኢትፍርሁኬ በኦሪት በነቢያት ካሉ በሃይማኖት በጥምቀት ያላችሁ እናንት ትበልጣላችሁና አይዟችሁ፡፡
አንድም አኮኑ ብለህ መልስ በሃይማኖት በጥምቀት ያሉ ሰዎች በምክረ ካህን በፈቃደ ካሀን ይኖሩ የለምን ወአሐቲ እምኔሆን በሃይማኖት በጥምቀት ካሉ ሰማያዊ አባታችሁ ሳያውቅ አንዱ አይጠፋም ወለክሙሰ እንዳለፈው ኢትፍርሁ በሃይማኖት በጥምቀት ካሉ በምክረ ካህን በፈቃደ ካህን ያላችሁ እናንተ ትበልጣላችሁና አትፍሩ።
                   ******   
፴፪፡ ኩሉ ዘየአምን ብየ በቅድመ ሰብእ አነኒ አአምኖ በቅድመ አቡየ ዘበሰማያት። ማር ፰፥፴፰፡፡ ሉቃ ፱፥፴፮፡፡ ፲፪፥፰፡፡ ፪፡ጢሞ ፪፥፲፪።
፴፪፡ በሰው ፊት ያመነብኝ ማለት ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ሳይል በሰው ፊት ያመነብኝን በሰማያዊ አባቴ ፊት ልጄ ወዳጄ እለዋለሁ።
                   ******   
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
17/08/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment