Tuesday, April 30, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 77

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲፩።
                    ******   
፩፡ ወሶበ ፈጸመ እግዚእ ኢየሱስ አዝዞቶሙ ለ፲ወ፪ቱ ኃለፈ እምህየ ከመ ይምሀር ወይስብክ ውስተ አህጉሬሆሙ።
                   ******   
፩፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርክቶስ ይኸን አስተምሮ ከፈጸመ በኋላ በየሀገራቸው ዙሮ ሊያስተምር ሔደ።
                    ****** 
በእንተ ኢየሱስ ወበእንተ አርዳኢሁ ለዮሐንስ መጥምቅ፡፡
፪፡ ወሰሚዖ ዮሐንስ ምዳባሮ ለእግዚእ ኢየሱስ እንዘ ሀሎ በቤተ ሞቅሕ ፈነወ ኀቤሁ ፪ተ እምአርዳኢሁ። ሉቃ ፯፥፲፰።
                    ******     
፪፡ ዮሐንስ መጥምቅ በግዞት ቤት ላለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ታምራት ያስተማረውን ትምርት የሠራውን ትሩፋት በሰማ ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ወደሱ ላከ አካውህ እሰጢፋኖስ ይባላሉ፡፡
                    ******     
፫፡ ወይቤሎ አንተኑ ዘትመጽእ፡፡
                    ******     
፫፡ ትመጣለህ ብለን ተስፋ የምናደርግህ አንተ ነህ
ወቦኑ ባዕድ ዘንሴፎ።
ወይም ይመጣል ብለን ተስፋ የምናደርገው ሌላ አለ ብሎ
(ሐተታ) እሱ ተጠራጥሮ አይደለም እኒህ ተጠራጥረው ነበርና አይተው አምላክነቱን ይረዱት ብሎ ነው እንጂ።
                    ******     
፬፡ ወአውሥአ ወይቤሎሙ ሐዊረክሙ ዜንውዎ ለዮሐንስ ዘርኢክሙ ወዘሰማዕክሙ።
                    ******     
፬፡ ሂዳችሁ ያያችሁትን የሰማችሁትን ለዮሐንስ ንገሩት ለዮሐንስ ልቡናችሁ ንገሩት
                    ******     
፭፡ ዕውራን ይሬዕዩ። ኢሳ ፴፭፥፭-፮፡፡
                    ******     
፭፡  ዕውራነ ሥጋ በተአምራት ዕውራነ ነፍስ በትምህርት ይድናሉ
ሐንካሳን የሐውሩ
ሐንካሳነ ሥጋ በተአምራት ሐንከሳነ ነፍስ በትምህርት ይድናሉ
እለ ለምጽ ይነጽሑ።
ልሙፃነ ሥጋ በተአምራት ልሙፃነ ነፍስ በትምህርት ይድናሉ
ወጽሙማን ይሰምዑ ።
ጽሙማነ ሥጋ በተአምራት ጽሙማነ ነፍስ በትምህርት ይሰማሉ
ወሙታን ይትነሥኡ።
ሙታነ ሥጋ በተአምራት ሙታነ ነፍስ በትምህርት ይነሣሉ።
ወነዳያን ይዜነዉ።
ይብዕሉ ሲል ነው ነዳያነ ሥጋ በተአምራት ነዳያነ ነፍስ በትምህርት ይከብራሉ።
                    ******     
፮፡ ወብፁዕ ውእቱ ዘኢተዓቅፈ ብየ።
                    ******     
፮፡ ነገር ግን ሰውነቴን አይቶ ዕሩቅ ብእሲ ያላለኝ ንዑድ ክቡር ነው።
(ሐተታ) ጌታ ገልጾ አምላክ እኔ ነኝ አላላቸውም እንዳንድ ፈላስፋ፡፡ አባቱ ሙቶ ያባቱን ቤተ ሰብና የሱን ቤተ ሰብ እየገዛ ሲኖር እየተጣሉ ቢያስቸግሩት ከፈላስፋ ሂዳችሁ ጠይቁልኝ ብሎ ሰዎች ላከ ሂደው ቢነግሩት ዝም አለ፡፡ ኋላ ካታክልት ቦታ ገብቶ የወራውን እየነቀለ ያልወራውን አፈር እያሳቀፈ ቈይቶ መጥቶ ተቀመጠ። ይነግረናል ብለው ቢያዩ  የማይነግራቸው ሆነ ተመልሰው ሄዱ ምን አላችሁ አላቸው። ቀንቶ ቢያየን ከመንገር በተቈጠረ ነበር አሉት። ያውቅለታልና ምን ሲያደርግ ነበር አላቸው። ሂደን ብንነግረው ዝም አለን። ኋላ ከተክል ቦታ ገብቶ የወራ የወራውን ነቅሎ ያልወራውን አፈር እያስታቀፈ ቈይቶ ተመልሶ ተቀመጠ። ይነግረናል ብለን ብናይ የማይነግረን ሆኖ መጣን አሉት። እናንተ ባታውቁት ነው እንጂ እሱስ ነግሯችኋል። የወራውን መንቀሉ ያባትህን ቤተ ሰብ አሰናብት ሲለኝ  ነው። ያልወራውን አፈር ማስታቀፉ ያንተን ቤተ ሰብ ገዝተህ ኑር ሲለኝ ነው ብሎ ያባቱን ቤተ ሰብ አሰናብቶ የሱን ቤተ ሰብ እየገዛ በጤና የሚኖር ሁኑዋል። እንደዚህም ሁሉ ያ ሥራ ሠርቶ አሳያቸው እንጂ ገልጾ እንዳልነገራቸው ጌታም ታምራት አድርጎ አሳያቸው እንጂ ገልጾ አምላክ እኔ ነኝ አላላቸውም።
                    ******     
ዘከመ ወደሶ እግዚእ ኢየሱስ ለዮሐንስ መጥምቅ።
፯፡ ወሶበ ኃለፉ እሉ ላዕካነ ዮሐንስ አኀዘ ይበሎሙ ለሕዝብ በእንተ ዮሐንስ መጥምቅ። ሉቃስ ፯፥፳፬፡፡
                    ******     
፯፡ ከዮሐንስ ተልከው የመጡት ከሄዱ በኋላ  የዮሐንስ መጥምቅን ነገር ለሕዝቡ ይነግራቸው ጀመር። ዮሐንስ መላኩ ተጠራጥሮ እንዳይደለ ሄደው ይረዱት ብሎ እንደ ሆነ፡፡ ሳሉ አለመናገሩ ከሄዱ በኋላ መናገሩ ቢሆን አመስግኖ ቢልከበት አመስግኖ ላከበት ባሉ ነበርና።
                    ******     
፰፡ ምንተኑመ ወፃእክሙ ገዳመ ትርአዩ።
፰፡ በገዳም ምን ልታዩ ወጥታችኋል።
                    ******     
   ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
22/08/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment