Sunday, April 28, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 76

====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
በከመ ተፈነዉ ሐዋርያት።
ምዕራፍ ፲።
                   ******   
፴፪፡ ኩሉ ዘየአምን ብየ በቅድመ ሰብእ አነኒ አአምኖ በቅድመ አቡየ ዘበሰማያት። ማር ፰፥፴፰፡፡ ሉቃ ፱፥፴፮፡፡ ፲፪፥፰፡፡ ፪፡ጢሞ ፪፥፲፪።
                   ******   
፴፪፡ በሰው ፊት ያመነብኝ ማለት ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ሳይል በሰው ፊት ያመነብኝን በሰማያዊ አባቴ ፊት ልጄ ወዳጄ እለዋለሁ።
                   ******
፴፫፡ ወለዘሰ ክህደኒ በገጸ ሰብእ አነኒ እክህዶ በገጸ አቡየ ዘበሰማያት።
                    ******   
፴፫፡ ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ብሎ በሰው ፊት ያላመነብኝን ግን እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት ወለድኩህ ካድኩህ እለዋለሁ፡፡
አንድም በቤተ ዮሴፍ ስበላ ስጠጣ አይቶ እሩቅ ብእሲ ነው ያላለኝን ልጄ ወዳጄ እለዋለሁ። ከቤተ ዮሴፍ ስበላ ስጠጣ አይቶ እሩቅ ብእሲ ያለኝን ግን በሰማያዊ አባቴ ፊት ወለድኩህ ካድኩህ እለዋለሁ፡፡
                    ******   
፴፬፡ ኢይምሰልክሙ ዘአምጻእኩ ሰላመ ለብሔር።
                    ******   
፴፬፡ ለሰው ፍቅርን አንድነትን ያመጣሁ አይምሰላችሁ ኢያምጻእኩ ይላል አላመጣሁም።
አላ መጥባሕተ ።
ሰይፍን ነው እንጅ ማለት ፀብን ክርክርን መለያየትን ነው እንጅ።
                    ******   
፴፭፡ ወመጻእኩሰ አፍልጥ ብእሴ እምአቡሁ።
                    ******   
፴፭፡ ወንድ ልጅን ከአባቱ፡፡
ወወለተኒ እምእማ።
ሴት ልጅን ከናቷ።
ወመርዓተኒ እምሐማታ።
መርዓትን ከአማቷ ልለይ መጥቻለሁ እንጅ።
(ሐተታ) አማትና ምራት ሳይስማሙ ከመሬት እንዲሉ የማይስማሙ ያሉ አይደለምን ቢሉ በሚስማሙት መናገር ነው።
አንድም ወመጻእኩ እፍልጥ ብእሴ እምአቡሁ ብለህ መልስ ወንጌልን ከኦሪት ወወለተኒ፤ አሠርቱ ቃላትን ከሥርዓት ረበናት ወመርዓተኒ ነቢያት ካህናትን ከምኵራብ ልለይ መጥቻለሁ እንጅ፤
አንድም ብእሴ እምአቡሁ ሰውን ከግብር አባቱ ከሰይጣን። ወወለተኒ ፈቃደ ነፍስን ከፈቃደ ሥጋ። ወመርዓተኒ ውሣጣዊት ግብርን ከአፍአዊት ግብር ልለይ መጥቻለሁ እንጅ።
                    ******   
፴፮፡ ወሰብአ ቤቱ ይጻረሮ ለሰብእ፡፡ ማር ፯፥፮፡፡
                    ******   
፴፮፡ ሰውን ቤተ ሰቦቹ ይጣሉታል ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ይዘህ መስለህ አትኖርም ይሉታል፡፡
አንድም መከራ እቀበላለሁ ባለ ጊዜ ሕዋሳቱ ይፈሩበታል
አንድም ሰብአ ቤቱ ይሁዳ ክርስቶስን ያሰቅለዋል።
                    ******   
፴፯፡ ዘያፈቅር አባሁ ወእሞ እምኔየ ኢይደሉ ሊተ ወኢይክል ይጸመደኒ። ሉቃ ፲፱፥፳፯።
                    ******   
፴፯፡ አባት እናት ክደዋል ልጆች አልካዱም። በሃይማኖት እናት አባቴን ካልመሰልኩ ርስቱን ጉልቱን ለሌላ ያወርሱብኝ የለም ብሎ በሃይማኖት ጊዜ ከኔ ይልቅ አባት እናቱን የወደደ ሰው የኔ ደቀ መዝሙር ሊባል አይገባውም እኔን ሊያገለግለኝ አይቻለውም።
ወዘያፈቅር ወልዶ ወወለቶ እምኔየ ኢይደሉ ሊተ።
አሁን ልጆች ክደዋል ኦባት እናት አልካዱም በሃይማኖት ልጆቼን ካልመሰልኋቸው ኋላ ማን ይረዳኛል ማን ያጸባኛል ብሎ በሃይማኖት ከእኔ ይልቅ ልጆቹን የወደደ የኔ ደቀ መዝሙር ሊባል አይገባውም፡፡
ወኢይክል ይጸመደኒ ።
ሊያገለግለኝ አይችልም።
                    ******   
፴፰፡  ዘኢያጥብዓ ወዘኢነሥአ መስቀለ ሞቱ ወዘኢተለወኒ ኢደደሉ ሊተ።
                    ******   
፴፰፡  ጨክኖ ነፍሱን ከሥጋው የሚለይበትን መከራ ተቀብሎ በመከራ ካልመሰለኝ የኔ ደቀ መዝሙር ሊባል አይገባውም።
                    ******   
፴፱፡ ዘረከባ ለነፍሱ ለይግድፋ። ሉቃ ፱፥፳፬፡፡ ፲፯፥፴፫፡፡ ዮሐ ፲፪፥፳፭፤
                    ******   
፴፱፡ በተፈጥሮ ያገኛት ሰውነቱን በሃይማኖት በጥምቀት ይጣላት
ወዘገደፋ ለነፍሱ በእንቲአየ ይረክባ።
በሃይማኖት በጥምቀት የጣላት ሰውነቱን ይረክባ በኀቤየ በኔ ዘንድ ጽድልት ብርህት ሆና ያገኛታል፡፡
አንድም ዘረከባ በሃይማኖት በጥምቀት ያገኛት ሰውነቱን በገራህተ መስቀል ይጣላት። ወዘገደፋ በእንቲአየ በኔ ስላመነ በገራህተ መስቀል የጣላት ሰውነቱን በክብር ያገኛታል።
                    ******   
፵፡ ዘኪያክሙ ተወክፈ ኪያየ ተወክፈ፡፡ ሉቃ ፳፥፲፮፡፡ ዮሐ ፲፫፥፳፡፡
                    ******   
፵፡ እናንተን የተቀበለ እኔን ተቀበለ ማለት እናንተን በተቀበለ እኔ አድርበታለሁ
ወዘኪያየ ተወክፈ ተወክፎ ለዘፈነወኒ።
እኔን የተቀበለም አባቴን ተቀበለ ማለት እኔ ባደርሁበት አባቴ ያድርበታል።
                    ******   
፵፩፡ ወዘተወክፈ ነቢየ በስመ ነቢይ አስበ ነቢይ ይነሥእ ።
                    ******   
፵፩፡  መምህሩን መምህር ብሎ የተቀበሉ መምህሩ የሚያገኘውን እኔ የምሰጠውን ዋጋ ያገኛል።
ወዘተወክፈ ጻድቀ በስመ ጻድቅ ዓስበ ጻድቅ ይነሥእ።
እውነተኛውን መምህር እውነተኛ መምህር ብሎ የተቀበለ መምህሩ የሚያገኘውን እኔ የምሰጠውን ዋጋ ያገኛል።
አንድም ዘተወክፈ ነቢየ።
ስለ አምላከ ኢሳይያስ ስለ አምላከ ኤርምያስ ብሎ ድሀውን የተቀበለ እኔ የምሰጠውን ነቢይ የሚያገኘውን ዋጋ ያገኛል። ከብተ ነቢ እንዲሉ
ወዘተወክፈ ጻድቀ ስለ አምላከ እንጦንስ ወመቃርስ ስለ አምላከ ተክለ ሃይማኖት ስለ አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ድኃውን የተቀበለ ጻድቁ የሚያገኘውን እኔ የምሰጠውን ዋጋ ያገኛል። ዝራዕ እክለከ ውስተ መቃብረ ጻድቃን ዕደው ጻድቃን የሀልው ውስተ ምሳህክ ወለእመ እግረ ጻድቃን ሐፀበት እንዲል።
አንድም ነቢየ ያነሥእ ለክሙ ተብሎ የተነገረልኝ እኔን እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ብሎ ያመነብኝ እኔ የምሰጠውን ዋጋ ያገኛል። ወዘተወክፈ ጻድቀ ብእሴ ጻድቀ ዘጽድቀ ይነግረክሙ እንዲል እውነተኛ መምህር የባሕርይ አምላክ ብሎ የተቀበለ እኔ የምሰጠውን ዋጋ ያገኛል።
                    ******   
፵፪፡ ወዘአስተየ ለ፩ዱ እምእሉ ንዑሳን ጽዋዓ ማይ ቈሪር ባሕቲቶ በስመ ረድእየ አማን እብለክሙ ኢየኃጕል ዓስቦ ማር ፱፥፵፡፡
                    ******   
፵፪፡ ቈሪር ቈሪረ ይላል ንዑሳን የብዕል የቊጥር ስለ አምላከ ጴጥሮስ ስለ አምላከ
ጳውሎስ ብሎ በኔ ካመኑ ምዕመናን ላንዱ ጽዋ ውሃ ያጠጣ ዋጋውን አያጣም ብዬ እንዳያጣ በእውነት እነግራችኋለሁ
(ሐተታ) ጠጅ ጠላ ሳለው አደደለም ባይኖረው ነው እንጂ። ሳለውስ እንዳይገባ ለማጠየቅ እመቦ ብእሲ ዘቦ ዝክር ሠናይ ወያበውእ በግዓ ንውረ ርጉም ውእቱ ትላለች ኦሪት ካልጀመሩት አይሆንምና ዘአስተየ አለ።
አንድም ወርቁንም ዕንቊንም ጽዋዓ ማይ በማለት ተናገረው የመንግሥተ ሰማይ ዋጋ አይሆንምና።
                    ******   
ምዕራፍ ፲፩።
፩፡ ወሶበ ፈጸመ እግዚእ ኢየሱስ አዝዞቶሙ ለ፲ወ፪ቱ ኃለፈ እምህየ ከመ ይምሀር ወይስብክ ውስተ አህጉሬሆሙ።
፩፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርክቶስ ይኸን አስተምሮ ከፈጸመ በኋላ በየሀገራቸው ዙሮ ሊያስተምር ሔደ።
                    ******     
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
21/08/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment