Thursday, March 28, 2019

ወንጌል ቅዱስ ክፍል 48


                 ====================
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል።
ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው።
ምዕራፍ ፭።
                  ******
፵፪፡ ወለኵሉ ዘሰአለከ ሀቦ። ዘዳ ፲፭፥፯-፰፡፡
                  ******
፵፪፡ ለለመነህ ሁሉ ስጠው።
ወለዘይፈድቅ ይትለቃሕ እምኔከ ኢትክልዖ። ካንተ ሊበደር የሚወደውን አትከልክለው፤ እንደ ዮሐንስ መሐሪ መጥተው አበድረን ሲሉት መክፈቻውን ሰጥቶ ወደዕቃ ቤቱ ይሰዳቸዋል የሚበቃቸውን ያህል ይዘው ይሔዳሉ። አምጥተው የሰጡት እንደሆነ ይቀበላል፡፡ ባይሰጡት ግድ የለውም ነበር።
                  ******
፵፫፡ ሰማዕክሙ ዘከመ ተብሀለ ለቀደምትክሙ አፍቅር ቢጸከ ወጽላእ ጸላኢከ፡፡ ዘሌ ፲፱፥፲፰፡፡
                  ******
፵፫፡ ከናንተ አስቀድሞ ለነበሩ ሰዎች ወዳጅህን ውደድ ጠላትህን ጥላ ያሏቸውን ሰምታችኋል። አፍቅር ቢጸከ ይሁን ጽላእ ጸላኢከ የሚል በኦሪት ወዴት አለ ቢሉ ባጸፋው ተናገረ፡፡ ወዳጅህን ውደድ ማለት ጠላትህን ጥላ ማለት ነውና።
አንድም ተጻረርዎሙ ለሜዶናውያን ኢትርስዖ ለአማሌቅ ያለውን ለውጦ አነበበው።
                  ******
፵፬፡ ወአንሰ እብለክሙ አፍቅሩ ጸላእተክሙ። ሉቃ ፮፥፳፯፡፡ ሮሜ ፲፪፥፴፡፡ ግብ፡ሐዋ ፯፥፶፱፡፡ ሉቃ ፳፫፥፴፬፡፡
                  ******
፵፬፡ እኔ ግን ጸላታችሁን ውደዱ እላችኋለሁ።
ወባርክዎሙ ለእለ ይሰድዱክሙ፡፡
ከሀገራችሁ አስወጥተው የሚሰዷችሁን መርቋቸው፡፡ ከቦታችሁ ከሀገራችሁ አያናውጣችሁ ከመንግሥተ ሰማያት አያውጣችሁ እያላችሁ።
ሠናየ ግበሩ ለእለ ይፃረሩክሙ፡፡
ለሚጣሏችሁ በጎ ሥራ ስሩላቸው።
ወጸልዩ በእንተ እለ ይትዔገሉክሙ።
ሥቃይ ለሚያጸኑባችሁ ጸልዩላቸው። እንዳንድ ምዕመን ዘመነ ዓላውያን ሁኖ አንድ ዓላዊ መከራ ያጸናበታል ጌታዬ ምረረ ገሃነምን ጣዕመ መንግሥተ ሰማያትን ባያውቅ እንጂ ነው። እንዲያውቅ አድርገው እያለ ይጸልይለታል ኋላ ዘመነ ዓላውያን አልፎ ዘመነ ክርስቲያን ሆነ፡፡ ያ ክርስቲያን ዛሬ ቢያገኘኝ እንደምን ያደርገኝ ነበር አለ። እሱስ ቀድሞም እንዲህ እያለ ይጸልይልህ ነበር አሉት። እኒህ ክርስቲያን ምግባራቸው የቀና መሆኑ ሃይማኖታቸው እንጂ የቀና ቢሆን ነው ብሎ ተመልሶ አምኖዋል ተጠምቋል።
                   ******
፵፭፡ ከመ ትኩኑ ውሉዶ ለአቡክሙ ዘበሰማያት።
                   ******
፵፭፡ የሰማያዊ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ማለት ሰማያዊ አባታችሁን ትመስሉ ዘንድ።
እስመ ውእቱ ያሠርቅ ፀሐየ ላዕለ ኄራን ወእኩያን።
ፀሐይን ለበጎዎችም ለክፉዎችም ያወጣልና።
ወያዘንም ዝናመ ላዕለ ጻድቃን ወኃጥአን፡፡
ዝናምን ለጻድቃንም ለኃጥአንም ያዘንማልና። ፀሐይ ሥጋው ደሙ ዝናም ወንጌል ነው፡፡ በእንቢተኝነታቸው ይቅርባቸው እንጂ ሥጋው ደሙ ወንጌል የተሠራ ለሁሉ ነውና።
                   ******
፵፮፡ ወእመሰ ዘአፍቀረክሙ ታፈቅሩ ምንትኑ ዕሤትክሙ።
                   ******
፵፮፡ የወደዳችሁንማ ብቻ ብትወዱ ዋጋችሁ ምንድነው።
አኮሁ መጸብሐንሂ ከማሁሰ ይገብሩ።
የወደዳቸውንማ ብቻ መውደድ አጣሮችስ ያደርጉት የለምን፡፡ ይህንስ አጣሮችም ያደርጉታል፡፡ ባንዱ አገር ያሉ አጣሮች ባንዱ አገር ካሉ ጋራ ይጠቃቀማሉና።
                   ******
፵፯፡  ወእመሂ ተአማኅክሙ ቢጸክሙ ባሕቲቶ ምንት እንከ ፍድፋዴ ገበርክሙ።
                   ******
፵፯፡ ወንድማችሁን ብቻ የምታከብሩ ከሆነ አብልጣችሁ ምን ትሩፋት ሠራችሁ። ምንት ፍድፋዴ ዘገበርክሙ፡፡ የሠራችሁት ትሩፋት ምንድነው።
አኮኑ አሕዛብኒ ከማሁሰ ይገብሩ፡፡
ወንድማቸውንማ ብቻ መወደድ አሕዛብስ ያደርጉት የለም ይህንስ አሕዛብም ያደር
ጉታል፡፡
                   ******
፵፰፡ አንትሙሰ ኩኑ ፍጹማነ ከመ አቡክሙ ሰማያዊ ፍጹም ውእቱ።
                   ******
፵፰፡ እናንተስ ሰማያዊ አባታችሁ ሁሉን አስተካክሎ በመውደድ ፍጹም እንደሆነ ሁሉን አስተከክላችሁ በመውደድ ፍጹማን ሁኑ።
                   ******
በእንተ ጾም ወጸሎት ወምጽዋት፡፡
ምዕራፍ ፮።
፩፡ ወባሕቱ ዑቁ ምጽዋተክሙ ኢትግበሩ ለዓይነ ሰብእ ከመ ያስተርእዩ ሎሙ።
፩፡ ባሕቱን የሚጽፍም የማይጽፍም አለ። ምጽዋታችሁን ሰው ይይልን ብላችሁ እንዳታደርጉ ዕወቁ።
                   ******
ይቆየን፡፡
**************
መልካሙ በየነ
ደብረ ማርቆስ፤ ኢትዮጵያ
20/07/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment