================

በእነዚህ ሃሳቦች
ላይ በሰፊው ተወያይተዋል፡፡ ሙያ በልብ ነው የሚሉ ሰዎች ከቆጋ ገዳም መነኮሳትን በጭራሽ ይዘን አንሄድም እነርሱን ይዘን ከሄድን
ጉዳያችን ቅብዓት ይመስላቸውና ሲኖዶስም አይፈርድልንም ያሉ ሲኾን ያበጠው ይፈንዳ የሚለው ቡድን ግን ወልደ አብ ለምን ተወገዘ?
የሚል ትልቅ ባነር እንደሚይዙም ተናግረዋል፡፡
በእውነት አደንቃችኋለሁ
ወልደ አብ ለምን ተወገዘ? የሚል ባነር ይዛችሁ ከመጣችሁ በጣም አደንቃችኋለሁ፡፡ ይህን ባነር ይዛችሁ የሊቃውንት ጉባዔን መሞገት
ከቻላችሁ እውነትም ሊቅ ናችሁ፡፡ እስኪ ባነሩን አሠሩት፡፡ እናንተ በወልደ አብ መወገዝ ብቻ አትገረሙ ገና ቀሪ ኹለቱ መጽሐፎቻችሁም
አብረው ይወገዛሉ፡፡ አሁን ወልደ አብ ለምን ተወገዘ? ብላችሁ መጠየቅ ካልቻላችሁ የቀሪዎቹን መወገዝም ትሰማላችሁ፡፡ ሊቃውንት ካሏችሁ
‹‹በወልደ አብ መናፍቅ አፈረ›› ብላችሁ ጭፈራ አይሉት መዝሙር ከምትጮኹ እስኪ በአደባባይ እንያችሁ፡፡ እስኪ የሊቃውንት ጉባዔን
ሞግቱ፡፡
‹‹አቡነ ማርቆስ
የልማት እና የወንጌል አባት ናቸው›› የሚል ባነር አሠርታችሁ ግን እንዳታሳፍሩን፡፡ ዓለም ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን ጉዳይ አንሥታችሁ
እንዳታፍሩ፡፡
======================
ጥቅምት
10/2011 ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ፣
ኢትዮጵያ
No comments:
Post a Comment